የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን አገልግሎት

እንኳን በሰላም መጡ ዲላ ከተማ አስተዳደር

ዲላ ከተማ የጌዴኦ ዞን አስተዳደር እና በደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት የግብርና ክላስተር መቀመጫ የሆነች እንግዳ ተቀባይ እና ውብ ናት።

አረንጓዴዋ ከተማ

215,870
ህዝብ
1,550
ከባህር ጠለል በላይ
20
ሙቀት
4.8%
አመታዊ እድገት

እንኳን ወደ ዲላ ከተማ በደህና መጡ

ዲላ ከተማ በደቡብ ኢትዮጵያ የምትገኝ ደማቅና እንግዳ ተቀባይ ከተማ ስትሆን፣ የዲላ ከተማ አስተዳደር እና የግብርና ክላስተር መቀመጫ በመሆን በመሆን በማገልግል ላይ ትገኛለች። 
ከአዲስ አበባ በስተደቡብ በግምት 360 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በአዲስ አበባ-ሐዋሳ-ሞያሌ ዋና መንገድ ላይ የምትገኘው ዲላ ለሰዎች፣ ለንግድ እና ለአዳዲስ እሳቤዎች ተፈጥሯዊ የመገናኛ ነጥብ ናት። ዲላ በመሠረተ ልማት፣ በሕዝብ አገልግሎቶች፣ በከተማ ልማት ዘርፎች እና በኮሊደር ልማት ቀጣይነት ባለው መሻሻል ምክንያት በሁሉም አቅጣጫዎች በፍጥነት በማደግ ላይ የምትገኝ ከተማ ናት። በተለይ ከተማዋ ለዓለም ገበያ በሚቀርበው እና ዓለም አቀፍ ዝና ባለው ኦርጋኒክ (ተፈጥሯዊ) የይርጋጨፌ ቡና በስፋት ትታወቃለች። 
 የከተማ አስተዳደሩ ለነዋሪዎች፣ ለጎብኝዎች እና ለልማት አጋሮች ምቹ እና ለኢንቨስትመንት ተስማሚ የሆነ አካባቢን በመፍጠር ረገድ ደህንነቷ የተጠበቀ፣ አረንጓዴ እና የበለፀገች ከተማ ለመገንባት በትጋት እየሰራ ይገኛል።
View Full Size

ራዕይ እና ተልዕኮ

ራዕይ

ዲላ ከተማ በደቡብ ኢትዮጵያ የብልጽግና እና የዘላቂ ዕድገት ምልክት፤ እንዲሁም የዕድል፣ የአካታችነት እና የላቀ የከተማ ኑሮ ጥራት የሚንፀባረቅባት ከተማ ሆና ማየት

ተልዕኮ

1

የዲላን ገጽታ ለመገንባት፣ ኢንቨስትመንትን እና ትብብርን ለማሳደግ የአካባቢ፣ የአገር አቀፍ እና ዓለም አቀፍ አጋርነቶችን ማጠናከር።

2

በሁሉም የህዝብ አገልግሎቶች ፍትሃዊነትን፣ ግልጽነትን እና ተጠያቂነትን በማረጋገጥ መልካም አስተዳደርን ማስፈን።

3

ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅርበት በመተባበር ደረጃቸውን የጠበቁ፣ የከተማ ልማት አገልግሎቶችን ለዜጎች መስጠት።

የመሪዎች መልዕክቶች

የከንቲባ መልዕክት

ዶ/ር መስፍን ደምሴ

የዲላ ከተማ ከንቲባ

ዲላ ከተማ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ከሚገኙ ረጂዮ ፖሊሲ ከተሞች መካከል እንዷ ሰትሆን አሁን ላይ የክልሉ ግብርና ክላስተር ማዕከል የበርካታ ብሄር፤ብሄረሰቦች በአብሮነት የምኖሩባት ከተማ ነች። ከተማችን የመደመር መንግሥት ለከተሞች ዕድገት የሰጠው ትኩረት መነሻ የከተማችን ኢኮኖሚ እንዲነቃቃ እና ለነዋሪዎች ምቹ የቱሪስቶች መዳረሻ እንዲሆኑ እና ፀጋቸውን ለይተው እንዲያድጉ የተወሰደው እርምጃም ውጤት እያሳየ ይገኛል። በተለይም የኮሪደር ልማት ሥራው ከተማውን በማዘመን ለኑሮ ምቹ፣ጽዱ እና ውብ እንዲሆኑ በማድረግ የከተማችንን ገጽታ የሚቀይር መሰረት በመሆን በተለይም ከተሞችን በቴክኖሎጂ ለማዘመን እና አገልግሎቶችን ለማሳደግ በርካታ ሥራዎች እየተከናወነ ይገኛል። በገጠር እና በከተማ ያለውን የዘመናዊ አኗኗር ልዩነት በማጥበብ እንዲሁም ሁለንተናዊ የኢኮኖሚ ትስስር ማጠናከር እንዲቻል ጥረቶች እየተደረጉ ይገኛሉም። ከለውጡ በፊት ለከተሞች እድገት ትኩረት ባለመሰጠቱ፣ከተሞች በሚገባቸው መጠን እንዳያድጉ ምክንያት ሆነው የቆየው ቢሆንም ከተሞች የተለያዩ ማንነቶች፣እሳቤዎች፣ ዕውቀት፣ካፒታል እና ሀብት የሚንሸራሸሩባቸው መሆን ስላሉባቸው የመደመር መንግሥት ከተሞች ለሁሉም ዜጋ ምቹ መኖሪያ መሆን አለባቸው የሚል እሳቤን ይዞ የመጣውን እሳቤ በጋራ እውን በማድረግ ላይ የምንገኝና ስልጡን ከተማ (ስማርት ሲቲን) ለመፍጠር ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ ይገኛል። ከተሞች ለአየር ንብረት ለውጥ ተጋላጭ እንዳይሆኑ በትኩረትም እየተሰራ ስሆን ዲላ ከተማ አረንጓዴያማ ቦታዎችን በማልማት እና ምቹ መናፈሻዎችን እንዲሁም ከተማን የሚመጥኑ የኮሪደር ልማት ሥራዎች እየተሰራ ይገኛል፡፡ ውብ ከተሞች የሰው ልጆች የሥራ ውጤቶች በመሆናቸው መልካም ነገር ከሠራን ጥሩ፤ ለነዋሪው ምቹ እና የዘመኑ ከተሞችን ለማየትና ለማሳየት የበለጠ ጥረቶች ይቀጥላሉ። አመሰግናለሁ!

የመሪዎች መልዕክቶች

መልዕክት

አቶ መንግስቱ ተክሌ

የዲላ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ዋና ተጠሪ

ጽኑ አንድነት ለተከታታይ ድልና ለሁለንተናዊ ብልጽግና የተከበራችሁ የከተማችን፣የሀገራችን ህዝቦች፣የአካባቢያችን ነዋሪዎችና የልማት አጋሮቻችን፤ ኢትዮጵያ በጀመረችው የብልጽግና ጉዞ ውስጥ ትልቁ አቅማችን አንድነታችን ነው። ፓርቲያችን ብልጽግና ይፋ ያደረገው የ"ስንዴ ነዶ" ማንፌስቶ፣የተበታተነ ጉልበታችንን አስተሳስረን፣የተፈጥሮ ፀጋዎቻችንን አልምተንና ምርታማነታችንን አሳድገን ራሳችንን በራሳችን ለመቻል የገባነው ታላቅ ቃል ኪዳን ነው። መንግሥታችን በየደረጃው የሚገጥሙትን ተግዳሮቶች በጽናት እየተጋፈጠ የህዝቡን ደህንነትና ልማት የማረጋገጥ ታሪካዊ ኃላፊነት አለበት። ይህ ድህረ-ገጽ የለውጥ ጉዟችንን የምናጋራበት ግልጽነትን የምናሰፍንበትና የህዝባችንን ድምጽ የምንሰማበት መድረክ ነው። የ"ስንዴ ነዶው" ጥንካሬ በእያንዳንዳችን ትጋት ላይ የተመሰረተ በመሆኑ ለሀገር ግንባታው በንቃት እንድትሳተፉ ጥሪዬን አቀርባለሁ። ፈታኝ ሁኔታዎችን ወደ አጋጣሚ በመቀየር፣ ኢትዮጵያን የብልጽግና ማማ ላይ እናወጣታለን! ኢትዮጵያ በልጆቿ ጥረት ታፍራና ተከብራ ለዘላለም ትኑር!

ቀጥታ ስርጭት

የዲላ ከተማ የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት

የከተማውን ወቅታዊ ማስታወቂያዎች፣ ፕሮጀክቶች እና የህዝብ መረጃዎች በቀጥታ ይከታተሉ።

የዲላ ከተማ የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት ከ7 ሰዓት በፊት
Facebook post image 1 Facebook post image 2 Facebook post image 3
Facebook post image 4
+1

"የክልሉ መስተዳድር ምክር ቤት በ30ኛ መደበኛ ጉባኤው በቀጣይ 30 ቀናት እቅድ ስራዎች ዙሪያ በመምከር አቅጣጫ አስቀመጠ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት መስተዳድር ምክር ቤት በበይነ መረብ ባካሄደው 30ኛ መደበኛ ጉባኤው ከምርጫ ማግስት ባለው የአንድ ወር የቅድመ መንግስት ምስረታ ወቅት በሚከናወኑ የቀጣይ የአንድ ወር ስራዎች ዕቅድ ዙሪያ በመምከር ቀጣይ አቅጣጫን አስቀምጧል፡፡ በጉባኤው የክልሉን መንግስት የ2018 ያለፉ አስር ወራት አጠቃላይ ስራዎች ዕቅድ አፈፃፀም እንዲሁም እንደ ሀገር በወጥነት ለማሳካት የታለሙ ሀገራዊ የልማት ኢንሼቲቮች ታሳቢ ያደረገ የቀጣይ የአንድ ወር ስራዎች መሪ ዕቅድ ቀርቦ ሰፊ ውይይት ተደርጎበታል፡፡ ርዕሰ መስተዳድሩ በውይይቱ ወቅት፡- በ7ኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ ህዝቡ በቅድመ ምርጫና በምርጫው ሂደት ያሳየው አስደናቂ ንቁ ተሳትፎ እንዲሁም በድህረ ምርጫው የታየው ስክነትና ጨዋነት ምርጫው ፍጹም ሰላመዊ በሆነ መንገድ ዴሞክራሲያዊ ሂደቱን ጠብቆ በስኬት እንዲጠናቀቅ ማስቻሉን ገልፀው፤ ዕውቅናና ምስጋና ይገባዋል ሲሉ ተናግረዋል፡፡ በቅድመ ምርጫው የተሰሩ ስራዎች ሀገራዊ ምርጫውን እጅግ ሰላማዊ፤ ነፃ፤ ፍትሃዊ፣ ታአማኒ እና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ በስኬት እንዲጠናቀቅ አስትዋፅኦ ማበርከቱን ጠቅሰው፤ የህዝቡን ሰላማዊና ጨዋነት የተሞላው ተሳትፎን ጨምሮ በሂደቱ የድርሻቸውን ለተውጡ አካላት በሙሉ ምስጋና አቅርበዋል፡፡ ርዕሰ መስተዳድሩ አጠቃላይ የምርጫው ውጤት በብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ተገልጾ የመንግስት ምስረታ እስከሚካሄድ ምንም መዘናጋት ሳይፈጠር በምርጫው አስደናቂ አኩሪ ተግባር የፈጸመው ህዝባችንን በልማትና በመልካም አስተዳደር ስራዎች ለመካስ በልዩ ትኩረት መስራት እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡ ለዚህም የተጀመሩ የልማት ተግባራትን በማጠናከር ለህዝብ አዳጊ የልማት ጥያዌዎች ምላሽ መስጠት የሚያስችል በየዘርፉ የአንድ ወር እቅድ በማቀድ ለተግባራዊነቱ መረባረብ እንደሚገባ ተናግረዋል። አክለው እቅዱ በተለይ በክብር ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፤ በየዘርፉ እምርታ ለማስመዝገብ እንደ ሀገር የተቀመጡ ሀገራዊ ግቦችን እንዲሁም በንቅናቄና በመደበኛ የሚመሩና የሚሰሩ ስራዎችን በመለየት እና ያሉ ተጨባጭ አቅሞችን ተጠቅሞ ፈጠራና ፍጥነት በታከለ አፈጻጸም ለውጤት ለማብቃት የሚያስችሉ ስልቶችን ታሳቢ ያደረገ ልሆን እንደሚገባም አስገንዝበዋል፡፡ ርዕሰ መስተዳድሩ የስራዎች አፈጻጸምን ለውጤት ለማብቃት በጠናካራ ድጋፍና ክትትል መደገፍ እንደሚገባም ጠቅሰው፤ በየደረጃው ያለው አመራር ከህዝብና ከመንግስት የተጣለበትን ከፍተኛ ኃላፊነት በአግባቡ በመወጣት፤ በቀሪ ጊዜያት የተሰነቁ ግቦችን ያለምንም መሸራረፍ በመፈጸምና በማስፈጸም የውጤት ዘላቂነትን ማረጋገጥ እንደሚገባው አሳስበዋል፡፡ መስተዳድር ምክር ቤቱ በስብሰባው በቀጣይ 30 ቀናት ሊሳኩ የሚገቡ እና በእጥፍ ለማሳደግ መሰራት የሚገባቸውን ተግባራት በመለየት ቀጣይ አቅጣጫ ያስቀመጠ ሲሆን ከነዚህም፡- * በግብርና ልማት ዘርፍ በቀሪ የበልግና የቀጣይ የመኸር እርሻ ስራዎች ምርታማነትን የማሳደግ፤ በሌማት ትሩፋት በእጥፍ የማብዛት እንዲሁም ለአረንጓዴ አሻራ ስራዎች በትኩረት መስራት፤ * የገቢ አሰባሰብ ስራዎችን በልዩ ትኩረት በቅንጅት በመምራትና ኢኮኖሚው ከሚያመነጨው ገቢ ፍትሀዊ ግብር በመሰብሰብ የህዝብ የልማት ጥያቄዎችን በብቃት ለመመለስ የሚስችል የውስጥ አቅምን የማጠናከር ተግባራት፤ * አገልግሎት አሰጣጥ የማዘመን ስራዎችን የማጠናከር በተለይም በዲላ እና በአርባ ምንጭ ከተሞች የተጀመሩ የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ማዕከላት ፈጥኖ በማጠናቀቅ ወደ አገልግሎት ማስገባት፤ እንዲሁም በሁሉም የከተማ አስተዳደሮች እንደየከተሞች ነባራዊ ሁኔታ በማስፋት በክልሉ የአገልግሎት አሰጣጥን በቴክኖሎጂ የተደገፈ፤ ፈጣንና ቀልጣፋ የማድረግ ተግባራት፤ * የተጀመሩ የከተሞች የኮሪደርና የወንዝ ዳርቻ ልማት ስራዎች በማጠናከር ከዳር የማድረስ እንዲሁም የገጠር ኮሪደር ልማትን በሁሉም የገጠር ቀበሌዎች በመጀመር የታለመውን የገጠር ሽግግር ለማሳካት እና የአርሶ አደሩን ህይወት በማሻሻል ተጠቃሚነቱን ለማረጋገጥ በትኩረት መስራት፤ * ለዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ቁልፍ የሆኑ የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ እና የ 5 ሚሊዮን የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና ግቦች ሙሉ በሙሉ ለማሳካት በልዩ ትኩረት መስራት፤ *በቱሪዝም ዘርፍ የክልሉን እምቅ አቅም መጠቀም በሚያስችል አግባብ በሁሉም ዞን እና ሪጂዮ ፖሊስ ከተሞች አዳዲስ የቱሪስት መዳረሻ ማዕከላትን መለየትና ማልማት፣ በኢንዱስትሪ ልማት ዘርፍ የተጀመሩ ተግባራትን ማጠናከር እንዲሁም አዳዲስ ኢንዱስትሪዎችን ለመጀመር የሚስችል ስራዎችን መስራት፤ በአጠቃላይ የኢኮኖሚ ሉዓላዊነት በማረጋገጥ ከተረጂነት የሚያልቅቁ ተግባራት፤ የኑሮ ውድነት ጫናን የመቀነስና ገበያ የማረጋጋት፤ የአደጋ ስጋት ተግባራት እንዲሁም የክልሉን ሰላም ለማፅናት የፀጥታ ስራዎች የማጠናከር ቀጣይ አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ መደበኛ ስብሰባውን አጠናቋል።"

የዲላ ከተማ የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት ከ9 ሰዓት በፊት
Facebook post image 1 Facebook post image 2 Facebook post image 3
Facebook post image 4
+4

"ክቡር አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) በዲላ ዙሪያ ወረዳ የግብርና ልማት ሥራዎችን ጎበኙ ዲላ፡ግንቦት፣26/2018 የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ክቡር ዶ/ር አበባየሁ ታደሰ በዲላ ዙሪያ ወረዳ ሽገዶ ቀበሌ በመገኘት የግብርና ልማት ሥራዎችን የመስክ ምልከታ አድርገዋል። ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ በመስክ ምልከታው ወቅት በወረዳው እየተከናወኑ ያሉ የቡና ክላስተር ልማት እና የሌማት ትሩፋት ሥራዎች አበረታች መሆናቸውን ጠቁመው ተግባሩ ይበልጥ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አሳስበዋል። የጌዴኦ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና የግብርና መምሪያ ኃላፊ ክቡር አቶ ተገኝ ታደሰ በበኩላቸው፤ በዞን ደረጃ የቡና ምርትና ምርታማነትን ለማሻሻል ለክላስተር ልማትና ለሌማት ትሩፋት ተግባራት ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። በዚህም በዲላ ዙሪያ ወረዳ በቡና ክላስተር ልማት ተጨባጭ ውጤቶች እየተመዘገቡ መሆኑን ጠቁመዋል። አቶ ተገኝ አክለውም የሌማት ትሩፋት ሥራዎች ጅምር የሚበረታታ መሆኑን ገልጸው በቀጣይም በሁሉም አካባቢዎች ይበልጥ ተጠናክረው መሰራት እንዳለባቸው አሳስበዋል። በዚሁ የመስክ ጉብኝት ላይ ክቡር አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ክቡር አቶ ተገኝ ታደሰን ጨምሮ የዞኑ ግብርና መምሪያ ምክትል ኃላፊዎች እንዲሁም የወረዳው ከፍተኛ አመራሮችና አስተባባሪ አካላት መሳተፋቸውን የዲላ ዙሪያ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ዘግቧል።"

የዲላ ከተማ የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት ከ10 ሰዓት በፊት
Facebook post image

"ምንም ዝርዝር መረጃ አልተሰጠም::"

የዲላ ከተማ የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት ከ14 ሰዓት በፊት
Facebook post image

"የጌዴኦ ዞን ከፍተኛ ፍ/ቤት በተከሳሽ በአቶ ጸጋዬ ታደሰ ላይ #የሞት ዉሳኔ አስተላለፈ ( #ዲላ ግንቦት 26/2018 ዓ/ም ) በከሳሽ አቃቤ ህግ እና በተከሳሽ በአቶ ጸጋዬ ታደሰ መካከል የነበረዉን የወንጀል ክስ መነሻነት የጌዴኦ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ግንቦት 17/2018 ዓ/ም በተከሳሹ ላይ መነሻ ቅጣት በሞት እንዲቀጣ በማለት የተከሳሹን የቅጣት ማቅለያ እና የዐ.ህግን የቅጣት ማክበጃ ለመስማት ለግንቦት 26/2018 ዓ/ም ቀጠሮ መያዙን መግለጻችን ይታወቃል። የጌዴኦ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት የወንጀል ችሎት ተከሳሽ ካቀረባቸዉ የቅጣት ማቅለያ ዉስጥ ሁለት የቅጣት ማቅለያን መቀበሉን ተመልክተናል በከሳሽ የጌዴኦ ዞን አቃቤ ህግ በተከሳሹ ላይካቀረባቸዉ ልዩ የቅጣት ማክበጃዎች ዉስጥ ሁለቱን ማክበጃዎች ፍርድ ቤቱ መቀበሉን ከስፍራዉ አረጋግጠናል የጌዴኦ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤትም ከተከሳሽ የቀረበዉን የቅጣት ማቅለያ እና አቃቤ ህግ ያቀረባቸዉን ልዩ የቅጣት ማክበጃ ተመሳሳይ እንደሆነ እንደሆነ ተረድቷል ስለዚህም የጌዴኦ ዞን ከፍተኛ ፍ/ቤት ግንቦት 26/2018 ዓ/ም በተከሳሹ ላይ ቀደም ብሎ የያዘዉን መነሻ ቅጣት የሞት ዉሳኔን አጽድቋል ፍርድ ቤቱም ዉሳኔዉን ተከታትሎ እንዲያስፈጽም ለዲላ ከተማ ማረሚያ ተቋም ትዕዛዝ መስጠቱን ከስፍራዉ የጌዴኦ ዞን ፖሊስ መምሪያ ህዝብ ግንኙነት ዘግቧል።"

የዲላ ከተማ የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት ከ1 ቀን በፊት
Facebook post image 1 Facebook post image 2 Facebook post image 3
Facebook post image 4
+2

"በዲላ ከተማ የሚገኙ 60 ምርጫ ጣቢያዎች ላይ ህዝቡ ያለምንም የጸጥታ ችግር በሰላማዊ መንገድ ድምጽ መስጠቱ ተገለጸ ዲላ፡ግንቦት፣25/09/2018 ዓ.ም በዲላ ሪጂዮ ፖሊስ ከተማ በ2 ክፍለ ከተማና 12 ቀበሌያት በሚገኙ 60 ምርጫ ጣቢያዎች ላይ ህዝቡ ዴሞክራሲያዊ መብቱን ተጠቅሞ ያለምንም የጸጥታ ችግር በሰላማዊ መንገድ ድምጽ መስጠቱን የዲላ ከተማ ሠላምና ጸጥታ መምሪያ ኃላፊ አቶ አለማየሁ ጂክሶ ተናግረዋል። አቶ አለማየሁ አክለውም የመጡ ውጤቶችን በጸጋ በመቀበል ወጣቶችም ሆኑ መላው የማህበረሰብ ክፍሎች በድምጽ መስጫ ወቅት ያሳዩትን ጨዋነት ማስቀጠል እንደሚገባቸው ገልጸው ህብረተሰቡም ሆነ የጸጥታ ተቋማቱ በሰላም ምርጫውን በማከናወናቸው የጸጥታ አካላትን አመስግነዋል። በተያያዘ ዜና በጌዴኦ ዞን በሚገኙ ሁሉም ምርጫ ጣቢያዎች ምርጫው በሰላማዊ መንገድ መጠናቀቁ ታውቋል። የጌዴኦ ዞን ሰላምና ጸጥታ መምሪያ ኃላፊ አቶ ሽብሩ ሚጁ እንደገለጹት 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ፍጹም ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ግብ ጥለው መንቀሳቀሳቸውን ተናግረዋል። በዞኑ በሚገኙ 5 መቶ 47 ምርጫ ጣቢያዎች ላይ ሂደቱ ያለ አንዳች የጸጥታ ችግር መጠቃለሉን የገለጹት አቶ ሽብሩ ከዞን እስከ ቀበሌ የጸጥታውን ሥራ በተገቢው መንገድ ያከናወኑ ሰላም አስከባሪዎችን አመስግነዋል።"

የዲላ ከተማ የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት ከ1 ቀን በፊት
Facebook post image 1 Facebook post image 2 Facebook post image 3
Facebook post image 4
+4

"የዲላ ከተማ የአስፓልት እና የኮሪደር ልማት ሥራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ አበባየሁ ታደሴ (ዶ/ር) አሳሰቡ ዲላ፡ግንቦት፣25/2018ዓ.ም በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በዲላ ከተማ አስተዳደር የታቀዱ የአስፋልት እና የኮሪደር ልማት ግንባታ ሥራዎች ይበልጥ ተጠናክረው እንዲቀጥሉ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አበባየሁ ታደሴ (ዶ/ር) አሳሰቡ። ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ በዲላ ከተማ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎችን የገመገሙ ሲሆን በቀጣይ ልዩ ትኩረት በሚሹ ጉዳዮች ላይም ከባለድርሻ አካላት ጋር የጋራ ውይይት አካሂደዋል። በውይይቱ ላይ አበባየሁ ታደሴ (ዶ/ር) እንደገለጹት እስካሁን ባለው ሂደት በተቋራጩ በኩል የተደረገው ቅድመ ዝግጅትና ለአስፋልት ግንባታ የሚውል የኮንስትራክሽን ግብዓት አቅርቦት አፈጻጸም መልካም የሚባል እንደሆነ አንስተዋል። በከተማዋ የተጀመሩ የኮሪደር ልማት ሥራዎች የዲላን ገጽታ ከመቀየር ባለፈ ለሕዝቡ ያላቸው ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ የጎላ መሆኑን ምክትል ርዕሰ-መስተዳድሩ ጠቅሰዋል። በመሆኑም እነዚህ የልማት ሥራዎች በሚቀጥሉት ጊዜያት በፍጥነትና በጥራት መከናወን እንዳለባቸው አሳስበዋል። ለዚህም ከክልሉ ዲዛይንና ሱፐርቪዥን ኢንተርፕራይዝ ጋር በጋራ በመሥራት ግንባታዎቹ በተያዘላቸው የጊዜ ሰሌዳ መሠረት ተጠናቀው ለሕዝብ አገልግሎት ክፍት መሆን እንዳለባቸው አስገንዝበዋል። የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ዲዛይንና ሱፐርቪዥን ኢንተርፕራይዝ ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር አብድሳ ኩፎ በበኩላቸው የአስፋልትና የኮሪደር ልማት ሥራዎቹ በተቀመጠላቸው የጊዜ ገደብ እንዲጠናቀቁ ለማድረግ ተቋማቸው የበኩሉን ኃላፊነት እንደሚወጣ አረጋግጠዋል። ኢንተርፕራይዙ የተጣለበትን የማማከር፣የቅርብ ክትትልና የቁጥጥር ሥራ በትጋት እንደሚወጣ ሥራ አስኪያጁ አስታውቀዋል። የዲላ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ መስፍን ደምሴ (ዶ/ር) በበኩላቸው የከተማ አስተዳደሩ ፕሮጀክቶቹ ያለምንም መስተጓጎል በተቀመጠላቸው የጥራት ደረጃ እንዲጠናቀቁ አስፈላጊውን የቅርብ ድጋፍና ክትትል እንደሚያደርግ ከንቲባው አረጋግጠዋል።"

የኢንቨስትመንት እድሎች

ከተማዋ ውስጥ ያሉ የኢንቨስትመንት ዘርፎች

በዘርፉ ያሉ እድሎች

አገልገሎቶች

ቅድሚያ የተሰጠው ዘርፍ

እንዱስትሪዎች

ግብርና

ማኑፋክቸሪንግ

ዋና የማስተዋጽኦ አጋጣሚዎች

  • ፈጣን አገልግሎት
ሴክተሮች

መምሪያዎች

የዲላ ከተማ አስተዳደር የሴክተር መ/ቤቶችና ሥራና ኃላፊነት

ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት ጽ/ቤት

ማዘጋጃ ቤታችን የከተማዋን ነዋሪዎች የኑሮ ጥራት ለማሻሻል፣ ጽዱና ለሚኖሩባት ምቹ የሆነች ከተማ ለመፍጠር የተለያዩ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና መሠረተ-ልማታዊ አገልግሎቶችን ይሰጣል። የፕላን መረጃ መስጠት፡መሬቱ ለምን አይነት አገልግሎት (ለቤት፣ ለንግድ፣ ለኢንዱስትሪ...) እንደሚ...
ዝርዝር ይመልከቱ

የመሬት አስተዳደር መምሪያ

መምሪያው በከተማ የሚገኘውን የከተማና የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀምን በበላይነት የማስተዳደርና የመቆጣጠር ኃላፊነት አለበት። በዚህም መሠረት፡-  የከተማ አጠቃላይ የመሬት ካዳስተር ሥርዓት በማዘመን ለዜጎች የይዞታ ማረጋገጫና የባለቤትነት መብት ሰነድ በቀልጣፋና በተመጣጣኝ ዋ...
ዝርዝር ይመልከቱ

የንግድና ኢንዱስትሪ ልማት መምሪያ

መምሪያው በከተማ የንግድና ኢንዱስትሪ ዘርፍ እድገትን በማምራት፣ በማበረታታትና በመቆጣጠር ረገድ ወሳኝ ሚና ይጫወታል። በዚህም መሠረት፡-  ቀልጣፋና ግልጽ የንግድ ምዝገባና ፈቃድ አሰጣጥ አገልግሎት በመስጠት ሕጋዊ የንግድ አካላት እንዲቋቋሙና እንዲስፋፉ ያደርጋል፤  በከተማ ውስጥ...
ዝርዝር ይመልከቱ

የቱሪዝም መምሪያ

መምሪያው የዲላ ከተማን በሀገር ውስጥም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተመራጭ የቱሪስት መዳረሻ ለማድረግ ይተጋል። በዚህም መሠረት፡-  የከተማዉን የቱሪዝም ሀብቶች (ተፈጥሯዊ፣ ባህላዊ፣ ታሪካዊ) በመለየት ካርታ በማዘጋጀትና በማስተዋወቅ ለቱሪስቶች ማራኪ እንዲሆኑ ያደርጋል፤ በከተማ ው...
ዝርዝር ይመልከቱ

የሥራና ክህሎት መምሪያ

መምሪያው በከተማ ውስጥ ምርታማ የሥራ ዕድሎችን በመፍጠርና የሰው ኃይልን ብቃት በማሳደግ ረገድ ማዕከላዊ ሚና ይጫወታል። በዚህም መሠረት፡-  የከተማ የሥራ ገበያ ፍላጎት በማጥናት በቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች የሚሰጠው ሥልጠና ከገበያ ፍላጎት ጋር እንዲጣጣም ያደርጋል፤  የሥራ አጦችን...
ዝርዝር ይመልከቱ

የፋይናንስና ፕላን ልማት መምሪያ

መምሪያው የከተማን የበጀት አዘገጃጀት፣ አፈጻጸምና ቁጥጥር በበላይነት የሚመራ ከፍተኛ አካል ነው። በዚህም መሠረት፡-  የከተማ ዓመታዊ በጀት በማዘጋጀት ለከተማ አስተዳደር ምክር ቤት በማቅረብ ሲፀድቅም አፈጻጸሙን ይከታተላል፤ ከክልል ፋይናንስ ቢሮ ጋር በመተባበር የከተማ የገንዘብ...
ዝርዝር ይመልከቱ

የገቢዎች መምሪያ

መምሪያው በከተማ የሚገኙ የተለያዩ የመንግሥት ገቢዎችን በመሰብሰብና በማስተዳደር ረገድ ወሳኝ ኃላፊነት አለበት። በዚህም መሠረት፡-  በከተማ ውስጥ ተፈጻሚነት ያላቸውን የክልል ታክስና ግብሮች (እንደ በጀት ዓመታዊ ታክስ፣ የንብረት ታክስ፣ ወዘተ) በመለየት በሥርዓት መሰብሰባቸውን...
ዝርዝር ይመልከቱ

የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ መምሪያ

መምሪያው በከተማ የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን በማስፋፋትና የፈጠራ ሥራዎችን በማበረታታት ረገድ ያተኩራል። በዚህም መሠረት፡-  በከተማ የሚገኙ መምሪያዎችና የበታች አስተዳደሮች የኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ (አይሲቲ) አጠቃቀም አቅም እንዲያድግ ድጋፍና ሥልጠና ይሰጣል፤  የከተማ አ...
ዝርዝር ይመልከቱ

ኮርደር ልማት

እንደ ሐገር በከተሞች ብቻ ሳይሆን በገጠርም ጭምር እየተተገበረ የሚገኘው የኮሪደር ልማት ቀድሞ የነበሩ ከተሞችን ገፅታ በመቀየር አዲስ ገፅታን በማላበስ ከተሞችን ውብ ማራኪና ተመራጭ እንዲሆኑ አስችሏል፡፡

የኮሪደር ልማት አዲስ ኢንሼቲቭ እንደመሆኑ በአተገባበር ወቅት ዉስን ተግዳሮቶች ቢያጋጥሙትም አሁን ላይ በመንግስት ብቻ ሳይሆን በሕብረተሰቡ ተሳትፎም ጭምር ተግባራዊ በመደረግ ላይ ይገኛል

ይህ አዲስ ከተማ ፈጣሪ ኢንሼቲቭዲላ ከተማን ለነዋሪዎች ለኑሮ ምቹ እንዲሁም ተወዳደሪ ከተማ ለማድረግ እየተተገበሩ ካሉ ሥራዎች መካከል አንዱ በተመረጡ የከተማዋ አካባቢዎች የመንገድ ኮሪደር ልማት መከወን ነው።

ባለፉት ዓመታት በከተማችን የመንገድ ኮሪደር ልማት የሚከወንባቸው በቁጥር 8 ዋና ዋና ኮሪደሮችን 18 ኪ.ሜትር በላይ በመለየት የፕላን ማስጠበቅ እንዲሁም ዘርፈ ብዙ የኮሪደር ልማት ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ፡

ለኮሪደር ልማት ሥራ የመጀመሪያው ቅድመ ሁኔታ የከተማ ፕላን የማስጠበቅ ሥራ ሲሆን በዚህመ ረገድ በከተማው ነዋሪ ንቁ ተሳትፎ እንዲሁም በየደረጃው ባሉ ባለድርሻ አካላት የተቀናጀ ሥራ ከ19.2 ኪሎሜትር በላይ ፕላን የማስጠበቅ ተግባር ተከናውኗል፡፡

የከተማው ነዎሪዎች በፕላን ማስጠበቅ ተግባሩ ባደረጉት ንቁ ተሳትፎ ከመንግሥት ሊወጣ የነበረውን 654 ሚሊዮን ብር ማዳን የተቻለ ሲሆን 517 ቤቶችን በማፍረስ የከተማ ፕላን ማሰጠበቅ ተግባር በማከናወን ለቀጣይ የመንገድ ኮሪደር ልማት ምቹ ሁኔታ መፍጠር ተችሏል፡፡

ከአዲስ አበባ ሞጆ ኢትዮ ኬኒያ የሚዘልቀው አስፋልት መንገድ አቋርጧት የሚያልፈው  የዲላ ከተማመግቢያበር ላይ እጅግ ሳቢና ማራኪ የመግቢያ ግንባታ የማጠናቀቂያ ሥራ በከናወን ላይ ይገኛል፡፡

በኮሪደር ልማት በመንገድ ዳር አረንጓዴ ልማት 16 ሺህ 700ካሬሜትርተሰርቶ የተጠናቀቀ ሲሆን በተመሳሳይ 8.4 Km እግረኛመንገድ ተጠናቋል፡፡

በቁጥር 5 እስናክሀውስግንባታ ተጠናቅቆ በእዚሁአከባቢ 20 ማረፊያ መቀመጫዎች ተዘጋጅተ ሕብረተሰቡ አረፍ ብሎ ነፋሻ አየር እንዲቀበልና ራሱን እንዲያዝናና አስተዋኦ በማበርከት ላይ ይገኛል፡፡

በከተማው የሚገኙ 2 አደባባዮችን ደረጃውን በጠበቀ መልኩ የማልማት እና የማስዋብ ሥራ ተሰርቶ 4ኪ.ሜ የመንገድ መብራት ማስዋብ ሥራ ተጀምሮ በመጠናቀቅ ላይ ይገኛል፡፡.

የኮሪደር ልማት ከተማን እንደ አዲስ ከነፍጠር ባሻገር ጊዜያዊና ቋሚ የስራ እድል በመፍጠርም አበርክቶቱ ከፍተኛ ሆኖ በዲላ ለ1ሺህ 205 ዜጎች ቋሚና ጊዜያዊ የሥራ ዕድል ተፈጥሯል፡፡

 

የዲላ ከተማ የኮሪደር ልማትን በማስቀጠል በከተማዋ ክልል ዋና ዋና መንገዶች ላይና አደባባዮች ብሎም ሰው ሰራሽ ሐይቅም ጭምር  በመስራት አዲስ ከተማ የመፍጠሩ ተግባር ከነዋሪዎቻችን ጋር እጅ ለእጅ በመያያዝ ተጠናክሮ ይቀጥላል፡፡

ኮርደር ልማት
ኮርደር ልማት
ኮርደር ልማት
ኮርደር ልማት
ኮርደር ልማት
ኮርደር ልማት

ዲላ በለውጥ ምዕራፍ ላይ ናት!

እንኳን ወደ ዲላ ከተማ አስተዳደር ይፋዊ የድረ-ገጽ መረጃ ቋት በሰላም መጣችሁ!

የከተማችን አስተዳደር ኮሚዩኒኬሽን ዋነኛ ዓላማ በመንግስትና በህዝብ መካከል የታመነ ድልድይ በመሆን፣ የዲላን ሁለንተናዊ እንቅስቃሴዎች ለነዋሪዎቻችንና ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ተደራሽ ማድረግ ነው።

ዲላ በለውጥ ምዕራፍ ላይ ናት!

በአሁኑ ወቅት በከተማችን በብልፅግና ፓርቲ መሪነት የሚከናወኑ፦

  • የኮሪደር ልማት ስራዎች፣
  • የውስጥ ለውስጥ መንገዶች ግንባታ እና
  • ሌሎች ግዙፍ የመሠረተ ልማት ስኬቶች የከተማችንን ገጽታ ከመቀየር ባለፈ ለነዋሪዎቻችን ምቹ የኑሮ ሁኔታን እየፈጠሩ ይገኛሉ።

የዲጂታል ሚናችንና ግባችን፦

  1. ወቅታዊ መረጃ፦ የልማት ስራዎችንና የመንግስት ውሳኔዎችን በታማኝነት ማጋራት።
  2. የመረጃ ሉዓላዊነት፦ በከተማችን ሰላምና ልማት ላይ የሚነዙ የተዛቡ መረጃዎችን (Misinformation) በእውነተኛ መረጃ መመከት።
  3. ሁለትዮሽ ግንኙነት፦ የመንግስትን ድምፅ ማስተማር ብቻ ሳይሆን፣ የህዝቡን ቅሬታና ጥቆማ የምንቀበልበት ክፍት መድረክ መሆን።

የክብር ጥሪ፦

የዲላ ከተማ ነዋሪዎችና የከተማችን ወዳጆች በሙሉ፤ ይህንን ድረ-ገጽ እንደ ዋነኛ የመረጃ ምንጭ በመጠቀም ለከተማችን ዕድገትና ሰላም ገንቢ አስተያየታችሁን እንድታካፍሉን ጥሪዬን አቀርባለሁ።

መረጃ የልማት መነሻ ነው!

 

ዲላ በለውጥ ምዕራፍ ላይ ናት!

የፎቶግራፍ አምዶች

የከተማችንን ውበት ያስሱ