የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን አገልግሎት

እንኳን በሰላም መጡ ዲላ ከተማ አስተዳደር

ዲላ ከተማ የጌዴኦ ዞን አስተዳደር እና በደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት የግብርና ክላስተር መቀመጫ የሆነች እንግዳ ተቀባይ እና ውብ ናት።

አረንጓዴዋ ከተማ

215,870
ህዝብ
1,550
ከባህር ጠለል በላይ
20
ሙቀት
4.8%
አመታዊ እድገት

እንኳን ወደ ዲላ ከተማ በደህና መጡ

ዲላ ከተማ በደቡብ ኢትዮጵያ የምትገኝ ደማቅና እንግዳ ተቀባይ ከተማ ስትሆን፣ የዲላ ከተማ አስተዳደር እና የግብርና ክላስተር መቀመጫ በመሆን በመሆን በማገልግል ላይ ትገኛለች። 
ከአዲስ አበባ በስተደቡብ በግምት 360 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በአዲስ አበባ-ሐዋሳ-ሞያሌ ዋና መንገድ ላይ የምትገኘው ዲላ ለሰዎች፣ ለንግድ እና ለአዳዲስ እሳቤዎች ተፈጥሯዊ የመገናኛ ነጥብ ናት። ዲላ በመሠረተ ልማት፣ በሕዝብ አገልግሎቶች፣ በከተማ ልማት ዘርፎች እና በኮሊደር ልማት ቀጣይነት ባለው መሻሻል ምክንያት በሁሉም አቅጣጫዎች በፍጥነት በማደግ ላይ የምትገኝ ከተማ ናት። በተለይ ከተማዋ ለዓለም ገበያ በሚቀርበው እና ዓለም አቀፍ ዝና ባለው ኦርጋኒክ (ተፈጥሯዊ) የይርጋጨፌ ቡና በስፋት ትታወቃለች። 
 የከተማ አስተዳደሩ ለነዋሪዎች፣ ለጎብኝዎች እና ለልማት አጋሮች ምቹ እና ለኢንቨስትመንት ተስማሚ የሆነ አካባቢን በመፍጠር ረገድ ደህንነቷ የተጠበቀ፣ አረንጓዴ እና የበለፀገች ከተማ ለመገንባት በትጋት እየሰራ ይገኛል።
View Full Size

ራዕይ እና ተልዕኮ

ራዕይ

ዲላ ከተማ በደቡብ ኢትዮጵያ የብልጽግና እና የዘላቂ ዕድገት ምልክት፤ እንዲሁም የዕድል፣ የአካታችነት እና የላቀ የከተማ ኑሮ ጥራት የሚንፀባረቅባት ከተማ ሆና ማየት

ተልዕኮ

1

የዲላን ገጽታ ለመገንባት፣ ኢንቨስትመንትን እና ትብብርን ለማሳደግ የአካባቢ፣ የአገር አቀፍ እና ዓለም አቀፍ አጋርነቶችን ማጠናከር።

2

በሁሉም የህዝብ አገልግሎቶች ፍትሃዊነትን፣ ግልጽነትን እና ተጠያቂነትን በማረጋገጥ መልካም አስተዳደርን ማስፈን።

3

ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅርበት በመተባበር ደረጃቸውን የጠበቁ፣ የከተማ ልማት አገልግሎቶችን ለዜጎች መስጠት።

የመሪዎች መልዕክቶች

የከንቲባ መልዕክት

ዶ/ር መስፍን ደምሴ

የዲላ ከተማ ከንቲባ

ዲላ ከተማ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ከሚገኙ ረጂዮ ፖሊሲ ከተሞች መካከል እንዷ ሰትሆን አሁን ላይ የክልሉ ግብርና ክላስተር ማዕከል የበርካታ ብሄር፤ብሄረሰቦች በአብሮነት የምኖሩባት ከተማ ነች። ከተማችን የመደመር መንግሥት ለከተሞች ዕድገት የሰጠው ትኩረት መነሻ የከተማችን ኢኮኖሚ እንዲነቃቃ እና ለነዋሪዎች ምቹ የቱሪስቶች መዳረሻ እንዲሆኑ እና ፀጋቸውን ለይተው እንዲያድጉ የተወሰደው እርምጃም ውጤት እያሳየ ይገኛል። በተለይም የኮሪደር ልማት ሥራው ከተማውን በማዘመን ለኑሮ ምቹ፣ጽዱ እና ውብ እንዲሆኑ በማድረግ የከተማችንን ገጽታ የሚቀይር መሰረት በመሆን በተለይም ከተሞችን በቴክኖሎጂ ለማዘመን እና አገልግሎቶችን ለማሳደግ በርካታ ሥራዎች እየተከናወነ ይገኛል። በገጠር እና በከተማ ያለውን የዘመናዊ አኗኗር ልዩነት በማጥበብ እንዲሁም ሁለንተናዊ የኢኮኖሚ ትስስር ማጠናከር እንዲቻል ጥረቶች እየተደረጉ ይገኛሉም። ከለውጡ በፊት ለከተሞች እድገት ትኩረት ባለመሰጠቱ፣ከተሞች በሚገባቸው መጠን እንዳያድጉ ምክንያት ሆነው የቆየው ቢሆንም ከተሞች የተለያዩ ማንነቶች፣እሳቤዎች፣ ዕውቀት፣ካፒታል እና ሀብት የሚንሸራሸሩባቸው መሆን ስላሉባቸው የመደመር መንግሥት ከተሞች ለሁሉም ዜጋ ምቹ መኖሪያ መሆን አለባቸው የሚል እሳቤን ይዞ የመጣውን እሳቤ በጋራ እውን በማድረግ ላይ የምንገኝና ስልጡን ከተማ (ስማርት ሲቲን) ለመፍጠር ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ ይገኛል። ከተሞች ለአየር ንብረት ለውጥ ተጋላጭ እንዳይሆኑ በትኩረትም እየተሰራ ስሆን ዲላ ከተማ አረንጓዴያማ ቦታዎችን በማልማት እና ምቹ መናፈሻዎችን እንዲሁም ከተማን የሚመጥኑ የኮሪደር ልማት ሥራዎች እየተሰራ ይገኛል፡፡ ውብ ከተሞች የሰው ልጆች የሥራ ውጤቶች በመሆናቸው መልካም ነገር ከሠራን ጥሩ፤ ለነዋሪው ምቹ እና የዘመኑ ከተሞችን ለማየትና ለማሳየት የበለጠ ጥረቶች ይቀጥላሉ። አመሰግናለሁ!

የመሪዎች መልዕክቶች

መልዕክት

አቶ መንግስቱ ተክሌ

የዲላ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ዋና ተጠሪ

ጽኑ አንድነት ለተከታታይ ድልና ለሁለንተናዊ ብልጽግና የተከበራችሁ የከተማችን፣የሀገራችን ህዝቦች፣የአካባቢያችን ነዋሪዎችና የልማት አጋሮቻችን፤ ኢትዮጵያ በጀመረችው የብልጽግና ጉዞ ውስጥ ትልቁ አቅማችን አንድነታችን ነው። ፓርቲያችን ብልጽግና ይፋ ያደረገው የ"ስንዴ ነዶ" ማንፌስቶ፣የተበታተነ ጉልበታችንን አስተሳስረን፣የተፈጥሮ ፀጋዎቻችንን አልምተንና ምርታማነታችንን አሳድገን ራሳችንን በራሳችን ለመቻል የገባነው ታላቅ ቃል ኪዳን ነው። መንግሥታችን በየደረጃው የሚገጥሙትን ተግዳሮቶች በጽናት እየተጋፈጠ የህዝቡን ደህንነትና ልማት የማረጋገጥ ታሪካዊ ኃላፊነት አለበት። ይህ ድህረ-ገጽ የለውጥ ጉዟችንን የምናጋራበት ግልጽነትን የምናሰፍንበትና የህዝባችንን ድምጽ የምንሰማበት መድረክ ነው። የ"ስንዴ ነዶው" ጥንካሬ በእያንዳንዳችን ትጋት ላይ የተመሰረተ በመሆኑ ለሀገር ግንባታው በንቃት እንድትሳተፉ ጥሪዬን አቀርባለሁ። ፈታኝ ሁኔታዎችን ወደ አጋጣሚ በመቀየር፣ ኢትዮጵያን የብልጽግና ማማ ላይ እናወጣታለን! ኢትዮጵያ በልጆቿ ጥረት ታፍራና ተከብራ ለዘላለም ትኑር!

ቀጥታ ስርጭት

የዲላ ከተማ የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት

የከተማውን ወቅታዊ ማስታወቂያዎች፣ ፕሮጀክቶች እና የህዝብ መረጃዎች በቀጥታ ይከታተሉ።

የዲላ ከተማ የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት ከ5 ሰዓት በፊት
Facebook post image

"ወቅታዊ ጉዳዮችን አስመልክቶ ከኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት የተሰጠ መግለጫ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. ማለዳ ላይ፤ የመጀመሪያው የወገግታ ጭላንጭል በከፍታማዎቹ የኢትዮጵያ ተራሮች ላይ ፈንጥቆ ጨለማውን ሳይቀድ በፊት ኢትዮጵያውያን ረጃጅም ሰልፍ ተሰልፈዋል። በጅማ፣ በድሬዳዋ፣ በሐዋሳ፣ በባሕር ዳር እንዲሁም ስማቸው በዓለም አቀፍ የዜና ጋዜጣዎች ላይ ፈጽሞ ሊወጣ በማይችሉ ከተሞችና መንደሮች ውስጥ ያሉ ወንዶችና ሴቶች፤ ወሳኝ ተግባር ለመፈጸም በሰልፍ ቆሙ። ድምፅ ሰጡ! ይህንን ታሪካዊ ኃላፊነት ለመወጣት ከሃምሳ አራት ሚልዮን በላይ የሚሆኑ ዜጎች ተመዝግበው ነበር። ይህ ቁጥር ከአንዳንድ ሀገሮች አጠቃላይ ሕዝብ ቁጥር በላይ ነው። ይህ ምርጫ እውነተኛ ስለመሆኑ ጥያቄ ለሚያነሣ ለማንኛውም አካል ግልጽ እና የማያሻማ ምላሽ ሰጥቷል! ‎ ‎የኢትዮጵያ ሕዝብ ፍላጎት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከ52,000 ምርጫ ጣቢያዎች መካከል ከ50,188 በላይ የሚሆኑት በሰዓቱ ተከፍተው ቀኑን ሙሉ መራጮችን ሲያስተናግዱ እንደነበር አረጋግጧል። ከ42 የፖለቲካ ፓርቲዎች የተወጣጡ ከ10,438 በላይ ዕጩዎች እና 80 የግል እጩዎች በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና የክልል ምክር ቤት ወንበሮችን ለማሸነፍ ተወዳድረዋል። ይህ በማንኛውም ሊለካ በሚችል መሥፈርት በኢትዮጵያ ታሪክ ትልቁ እና በውሳኔ አሰጣጥም ሆነ በአስተዳደራዊ ረገድ እጅግ በረቀቀ ሁኔታ ተግባራዊ የተደረገ ዴሞክራሲያዊ ተሳትፎ የታየበት ኩነት ነበር። ‎ የቀድሞው የኬንያ ፕሬዚዳንት ክቡር ኡሁሩ ኬንያታ የሚመሩትና ከ37 የአፍሪካ ሀገሮች የተወጣጡ 83 ታዛቢዎችን ያቀፈው የአፍሪካ ኅብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን ምርጫውን “ዴሞክራሲያዊ አስተዳደርን በሰፊው በሚደግፍ ሕጋዊና ተቋማዊ ማዕቀፍ ውስጥ የተካሄደ” ሲል ገምግሞታል። በቀድሞዋ የኡጋንዳ ምክትል ፕሬዚዳንት ክብርት ዶክተር ስፔሲዮዛ ዋንዲራ ካዚብዌ የሚመራው የኢጋድ የምርጫ ታዛቢ ቡድን ባወጣው የመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርት፥ በታዘቡባቸው ጣቢያዎች ሁሉ የምርጫ ሳጥኖች በትክክል የታሸጉ መሆናቸውን፣ የፓርቲ ወኪሎች በሂደቱ በሙሉ መገኘታቸውን እንዲሁም ምርጫው አስደናቂ ተቋማዊ፣ አስተዳደራዊና የቴክኖሎጂ ዕድገትን ያሳየ መሆኑን አረጋግጧል። የኢጋድ የምርጫ ታዛቢ ልዑክ ይሄንን ምርጫ «የበርካታ አዳዲስ ምዕራፎች ምርጫ» ሲል ሰይሞታል። የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን በድምፅ መስጠት ሂደት ውስጥ ምንም ዓይነት የሰብዓዊ መብት ጥሰት እንዳልተመለከተ አረጋግጧል። የሲቪክ ማኅበረሰብ ታዛቢዎች ጥምረት በምርጫ ቦርድ እውቅና ከተሰጣቸው 55 ድርጅቶች 65,299 የታዛቢዎችን በመላ ሀገሪቱ ያሠማራ ሲሆን፥ 99 በመቶ የምርጫ ጣቢያዎች ላይ ያለምንም ዕንቅፋት የመታዘብ ዕድል ማግኘቱን አረጋግጧል። እነዚህ ተዓማኒነት ያላቸው ሀገራዊ እና አኅጉራዊ ተቋማት ያደረጓቸው ግምገማዎችና የሰጧቸው እውነተኛ ፍርዶች ናቸው። እነዚህ ለአፍሪካ ጥላቻ ካላቸው ወይም የአፍሪካን ዴሞክራሲ በውጫዊ መሥፈርቶች ከሚለኩ ተቋማት የተደመጡ ድምፆች አይደሉም። ‎ ‎አንዳንድ ዓለም አቀፍ ተንታኞች ይሄንን ምርጫ እንደ ንግሥና በዓል አድርገው ያቆሸሹት ሲሆን ውጤቱም አስቀድሞ የተወሰነ ድራማ እንደነበር አድርገው ሊያቀርቡት ሞክረዋል። እነዚህን መግለጫዎች ከእውነታው ፈጽሞ የራቁ፣ በጥናትና ትንተና ላይ ያልተመሰረቱ እንዲሁም ነፃና የታሰበበት ዴሞክራሲያዊ ምርጫቸውን በኩራት ላደረጉ በሚልዮን የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ክብር የማይሰጡ በመሆናቸው የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ሙሉ በሙሉ የማይቀበላቸው መሆኑን ያረጋግጣል። አስቀድሞ የተወሰነ ውጤት ቢኖር ኖሮ፤ ከ37 የአፍሪካ ሀገሮች የተወጣጡ 83 ገለልተኛ ታዛቢዎችን፣ 65,299 የሀገር ውስጥ የሲቪል ማኅበረሰብ ታዛቢዎችን ወይም 1,100 ዕውቅና የተሰጣቸውን ዓለም አቀፍ ጋዜጠኞች መጋበዝ ባላስፈለገ ነበር። ‎ ‎ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በዚህ ሀገራዊ ምርጫ ለተሳተፉ የኢትዮጵያ ዜጎች፣ ለብሔራዊ ምርጫ ቦርድ እና ላሠማራቸው ከ350,000 በላይ ኃላፊዎች፣ ሂደቱን ለጠበቁት የጸጥታ ኃይሎች እንዲሁም ኢትዮጵያ ለዴሞክራሲ ግንባታ መጎልበት እና ለሂደቱ መሳካት ያላትን ቁርጠኝነት ላረጋገጡት የአፍሪካ እና ቀጣናዊ የታዛቢ ቡድኖች ምስጋናቸውን ያቀርባሉ! ‎ ‎ስለ ኢትዮጵያ ልማት ‎ኢትዮጵያውያን ግንቦት 24 2018 ዓ.ም ውሳኔያቸውን ሲያስቀምጡ፣ ሀገራቸውን በፍጹም የዴሞክራሲ ባህል ውስጥ ለማንበር ነው። በሌላ በኩል ኢትዮጵያ ባላት ጸጋ ልክ የሚያስፈልጋትን ሁለንተናዊ ልማት በፍጥነት እውን የማድረግ ባህል እንዲቀጥል ሕዝባችን ተናግሯል። ‎ባለፉት ዓመታት የታየው እውነት እንደሚያሳየን የኢፌዴሪ መንግሥት የተስፋ ቃል መንግሥት አልነበረም። ይልቁንም በተጨባጭ የሚታዩ ውጤቶች የተመዘገቡበት ውጤት ተኮር መንግሥት ሲሆን፤ እነዚህም ውጤቶች በግልጽ የሚታዩ ናቸው። የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በ2017 በጀት ዓመት የ9.2 በመቶ ዕድገት ያስመዘገበ ሲሆን፥ ይሄም በዓለም ላይ ፈጣን ዕድገት ካስመዘገቡ ኢኮኖሚዎች አንዱ ያደርገዋል። ይሄንን መነቃቃት መሠረት በማድረግ በ2018 በጀት ዓመት የኢኮኖሚ ዕድገቱ 10.2 በመቶ ይደርሳል ተብሎ ይጠበቃል። ዕድገቱ ግብርናን፣ ኢንዱስትሪንና የአገልግሎት ዘርፎችን በከፍተኛ ደረጃ ያካተተ ሰፊ መሠረት ያለው ቢሆንም፥ ከጊዜ ወደ ጊዜ ግን ኢንዱስትሪው ለዕድገቱ ዋነኛ አንቀሳቃሽ ኃይል ሆኖ እየመጣ ይገኛል። ይሄም መንግሥት ለማኑፋክቸሪንግ፣ ለኢንዱስትሪ ልማት፣ ለዕሴት ጭማሪና ለውጭ ገበያ ተኮር ምርቶች የሰጠውን ቀጣይነት ያለው ትኩረት ያሳያል። ‎እነዚህ ውጤቶች እንዲሁ ግምቶች ብቻ ሳይሆኑ፥ በጠቅላይ ሚኒስትሩ የ100 ቀናት የሥራ አፈጻጸም ግምገማ ሥርዓት አማካኝነት ክትትል የሚደረግባቸው የተጠያቂነትና የታቀደ አመራር ፍሬዎች ናቸው። አጠቃላይ የወጪ ንግድ ገቢ 20 ቢልዮን የአሜሪካ ዶላር ይደርሳል ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን፥ ይህም ከ2016 ዓ.ም. ወዲህ የ100 በመቶ ገደማ ጭማሪ አሳይቷል። የዋጋ ግሽበትም ወደ ታች ማሽቆልቆሉን በመቀጠል አሁን ላይ ወደ አንድ አሐዝ ደረጃ እየተቃረበ ይገኛል፤ ይሄም በቅርብ ዓመታት ውስጥ በቤተሰቦችና በንግዶች ላይ ከባድ ጫና ፈጥሮ ከነበረው ባለ ሁለት አሐዝ የዋጋ ግሽበት አንጻር ትልቅ መሻሻል ነው። ይህ ስኬት የተመዘገበው ዓለም አቀፍ የኃይል አቅርቦትና ሌሎች ስትራቴጂካዊ ቁሳቁሶችን ገበያ ያናጋው የመካከለኛው ምስራቅ ወቅታዊ ጂኦፖለቲካዊ ውጥረት ጨምሮ፣ ውጫዊ ጫናዎች በነበሩበት ወቅት ነው። ‎የሀገር በቀል ኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳ ከተጀመረ ወዲህ መንግሥት ከውጭ ምንጮች ምንም ዓይነት አዲስ የንግድ ብድር ስምምነት ያላደረገ ሲሆን፥ ይሄም የሀገሪቱን የብድር ዕዳ ጫና በከፍተኛ ሁኔታ አቅልሎታል። ከእነዚህ ቁጥሮች በስተጀርባ ኢትዮጵያውያን በዓይናቸው የሚያዩትና በእጃቸው የሚዳስሱት ተጨባጭ ለውጥ አለ። ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ለመኖሪያ ቤቶች፣ ለንግድ ተቋማትና ለጎረቤት ሀገራት የኤሌክትሪክ ኃይል እያመነጨ ይገኛል። ይህ ግድብ በራሳቸው በኢትዮጵያውያን የተደገፈ፣ በኢትዮጵያውያን መሐንዲሶች የተገነባና ቀጣይነት የነበረውን ውጫዊ ጫናዎችን ተቋቁሞ የተጠናቀቀ ነው። ከሃይድሮ ፓወር ጎን ለጎን፥ በኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል የሚገኘውን የአይሻ ሁለት የንፋስ ኃይል ማመንጫ እና በአርሲ ዞን የሚገኘውን የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች፤ በመሳሰሉ ሥራዎች የታዳሽ ኃይል አቅርቦቷን እያሰፋች ሲሆን፥ ይህም የቀጣናዊ ኢነርጂ ትብብርን እያሳደገ የብሔራዊ ኃይል አቅርቦት መረቡን የመቋቋም ዐቅም ያጠናክራል። በአፍሪካ አህጉር ታሪክ ውስጥ ትልቁ የመሠረተ ልማት ኢንቨስትመንት አንዱ የሆነው የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ፕሮጀክት የመሠረት ድንጋይ ተጥሎ ግንባታው ተጀምሯል። እነዚህ ምኞቶች አይደሉም፤ ተጨባጭ ሐቆች ናቸው። ‎ ‎ግብርና፣ አምራች ኢንደስትሪና ቴክኖሎጂ ‎በግብርናው ዘርፍ፣ የመንግሥት የምግብ ሉዓላዊነት አጀንዳ ወቅታዊ ለውጦችን ሳይሆን መዋቅራዊ ውጤቶችን እያስገኘ ቀጥሏል። በሶማሌ ክልል የጎዴ ዩሪያ ማዳበሪያ ፋብሪካን ለመገንባት ከአሊኮ ዳንጎቴ ግሩፕ ጋር የተፈረመው አጋርነት የዘመኑ ጉልህ የኢንዱስትሪ ኢንቨስትመንቶች አንዱ ማረጋገጫ ነው። ፋብሪካው በዓመት 3 ሚልዮን ሜትሪክ ቶን ዩሪያ የማምረት አቅም እንዲኖረው ታቅዶ እየተገነባ ሲሆን፥ ይሄም ኢትዮጵያን በዓለም ትላልቅ ማዳበሪያ አምራች ሀገራት ተርታ ያሰልፋታል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ግንቦት 9 ቀን 2018 ዓ.ም. የፕሮጀክቱን የግንባታ ሂደት በጎበኙበት ወቅት እንደገለጹት፤ “ይህ ፕሮጀክት በግብርና ትራንስፎርሜሽን፣ በምግብ ዋስትና፣ በኢንዱስትሪ ዕድገትና በኢኮኖሚ ራስን መቻል ላይ የተደረገ ስትራቴጂካዊ ኢንቨስትመንት ነው” ብለዋል። አስተማማኝ ባልሆነና ውድ በሆነ የማዳበሪያ አቅርቦት ለረጅም ጊዜ ለተገደቡት ኢትዮጵያውያን አምራቾች የዚህ ፕሮጀክት ፋይዳ ፈጣንና ተጨባጭ ነው። ከዚህ ምርጫ ጥቂት ቀናት ቀደም ብሎ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ግንቦት 19 ቀን 2018 ዓ.ም. በነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ ምርቃት ላይ ሲገኙ የታየው ተምሳሌትነት ለቦረና ሕዝብ ትልቅ ትርጉም ነበረው። ይህ ዞን በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቅበት ስም የሀገርን አንገት ያስደፋ እንደነበር የቅርብ ጊዜ ትውስታ ሲሆን፤ እርሱም ድርቅ ነው። ለሦስት ተከታታይ ዓመታት የዝናብ መጥፋት በሚሊዮን የሚቆጠሩ ከብቶችን የገደለ፣ ቤተሰቦች ለውኃ ፍለጋ በመቶዎች የሚቆጠሩ ኪሎ ሜትሮችን እንዲጓዙ ያስገደደ፣ እንዲሁም በእነዚህ የግጦሽ መሬቶች ላይ ለዘመናት ራሳቸውን ችለው የኖሩ ማኅበረሰቦችን ለአስቸኳይ የምግብ እርዳታ እጅ እንዲዘረጉ አድርጎ ነበር። ዓለም የሚያውቃት ቦረና እርሷ ነበረች። የጠቅላይ ሚኒስትሩ የግንቦት ወር ጉብኝት ግን የተለየ ታሪክ አሳይቷል። አሁን ላይ ለአርብቶ አደር ማኅበረሰቦችና ለከብቶቻቸው ንጹሕ ውኃ እያቀረቡ ያሉትን የውኃና የመስኖ መሠረተ ልማቶችን የገመገሙ ሲሆን፥ ከጥቂት ዓመታት በፊት አቧራ ብቻ በነበረው መሬት ላይ የክላስተር እርሻዎችን ጎብኝተዋል፤ በያቤሎ የባህል ማዕከል መርቀዋል፤ እንዲሁም በአየር ንብረት ሁኔታዎች ምክንያት ቀድሞ ተገልሎ ለነበረው ቀጣና ዓመቱን ሙሉ ትስስር የሚፈጥር አውሮፕላን ማረፊያ መርቀው ከፍተዋል። ‎ ‎የአምራች ዘርፉም ተመሳሳይ የለውጥ ታሪክ አለው። በግንቦት 2018 ዓ.ም. በተካሄደው 4ኛው ኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ ላይ፤ መንግሥት ለአራት ዓመታት የተመዘገበውን ቀጣይነት ያለው የኢንዱስትሪ መስፋፋት ውጤቶች አቅርቧል። የአምራች ዘርፉ የግብአት አቅርቦት በዓመት 9 ሚልዮን ቶን ወደ 15 ሚልዮን ቶን አድጓል። የምርት አቅም አጠቃቀም ከ47 በመቶ ወደ 67 በመቶ ከፍ ማለቱን፣ የማኑፋክቸሪንግ ዕድገት ከ4.8 በመቶ ወደ 10.7 በመቶ ማደጉን፣ እንዲሁም ለአነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች የሚቀርበው ፋይናንስ ከ8.1 ቢልዮን ብር ወደ 50 ቢሊዮን ብር ማደጉን ያሳያል። እነዚህ ስኬቶች በሀገር ውስጥ ምርት ላይ በከፍተኛ ሁኔታ እየተንጸባረቁ ይገኛሉ። ኤክስፖው በተጠናቀቀ በሃያ ቀናት ውስጥ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዘጠኝ ወራት ውስጥ ብቻ ተጠናቆ ከ80 በመቶ በላይ ጥሬ ዕቃውን ከሀገር ውስጥ የሚያገኘውን ግዙፍ የኢንዱስትሪ ኢንቨስትመንት «ግራንዲዩር የሴራሚክ ማኑፋክቸሪንግ» ፋብሪካን በሞጆ ከተማ መርቀዋል። ቀደም ሲል በገቢ የሴራሚክ ምርቶች ላይ ጥገኛ የነበረችው ኢትዮጵያ አሁን ላይ የሴራሚክ ምርቶችን ከውጭ ማስገባት ሙሉ በሙሉ ለማቆምና ለውጭ ገበያ የሚሆን ምርት ለማስፋፋት እየተዘጋጀች ትገኛለች። ‎በቴክኖሎጂው ዘርፍም፥ ዘመናዊ ልማት ከጊዜ ወደ ጊዜ በዳታ፣ በፈጠራና በዲጂታል ሥርዓቶች የሚወሰን መሆኑን በመገንዘብ፥ መንግሥት ኢትዮጵያን ሰው ሠራሽ አስተውሎት እና የኢንዱስትሪ 5.0 ማሕቀፎችን ቀድመው ከተገበሩ ሀገራት ተርታ እያሰለፋት ይገኛል። ‎ ‎የጽንፈኝነትን ፖለቲካ ውድቅ ማድረግ ‎በኦነግ ሸኔ ዐማጽያን በንጹሐን ዜጎች ላይ በተለይም በሃይማኖት ተቋማት ውስጥ ዒላማ ተደርገው የተፈጸሙ ጥቃቶችን ተከትሎ፤ የቤተሰብ እና የወዳጆቻቸውን ሕይወት ላጡ፣ የአካል ጉዳት ለደረሰባቸው እና የቤት ንብረታቸው ለወደመባቸው በአርሲ ዞን ለሚገኙ ወገኖቻችን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በኢትዮጵያ መንግሥት ስም የተሰማቸውን ጥልቅ ኀዘን ይገልጻሉ። እነዚህ ጥቃቶች የሀገሪቱን ብሔራዊ ዕድገት ለማደናቀፍ ከሚሹ አካላት፣ በአማራ ክልል ከሚንቀሳቀሱ የሀገር ውስጥ አማፂ ቡድኖች እና ለሀገሪቱ ሁለንተናዊ ዕድገት ጥላቻ ካላቸው የውጭ ኃይሎች ጋር በጥምረት የተከናወኑ ሲሆኑ፤ ዓላማቸውም በኢትዮጵያ አለመረጋጋትንና የምርጫ መስተጓጎልን ለመፍጠር ሲደረግ የነበረ የጥፋት ውጥን ተከታይ ነው። መንግሥት 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ያለ አንዳች የፀጥታ ችግር ፍትሐዊና አሳታፊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ከአንድ ዓመት በላይ የዘለቀ ልዩ ትኩረትና ዝግጅት በማድረግ በቁርጠኝነት ሲሠራ ቆይቷል። በሌላ በኩል የጥፋት ኃይሎች ከባዕዳን ጋር 'ፅምዶ' የሚል ቁርኝት በመፍጠር ዕኩይ ዓላማቸውን ለማሳካት ሰፊ የጥፋት ዝግጅት ሲያድርጉ ቆይተዋል፣ ሀገራዊ ምርጫው እንዳይከናወን ሰፊ ርብርብ አድርገዋል። በተጨባጭም በቅድመ ምርጫ እና በምርጫ ወቅት የዜጎችን የመምረጥ መብትና ነጻነት ለመጋፋትና ለማደናቀፍ አለን የሚሉትን የጥፋት እጅ ዘርግተዋል። ‎እነዚህ የጠላት ኃይሎች በመደጋገፍና በመናበብ ዐመፅና ሁከት ለማነሳሳት፣ ከተሞችን በሽብር ጥቃት ለማወክ፣ በመንገዶች የደፈጣ ጥቃት በመፈጸም እንቅስቃሴ ለመገደብ እና በተወሰኑ አካባቢዎች ዒላማ አድርገው ነጥሎ ለማጥቃት ተንቀሳቅሰዋል። እንደ ማሳያ የጦር መሣሪያ፣ ተተኳሾችንና ሌሎች ሎጀስቲክሶችን በድጋፍ በማቅረብ በደቡባዊ ትግራይ በሚገኙ አዋሳኝ የአማራ ክልል አንዳንድ ቦታዎች ላይ ትንኮሳ ፈጽመዋል፣ በአማራ ክልል ባሕር ዳር፣ ጎንደር፣ ደብረ ብርሃን እና ወልድያ ከተሞችን ጨምሮ በክልሉ ዋና ዋና ከተሞች እና ሲቪሎች ላይ ዒላማ በማድረግ ያካሄደው የሽብር እንቅስቃሴና ዝግጅት፣ በአዲስ አበባ ከተማ ባደራጃቸው የኅቡዕ ሴሎች አማካኝነት በተመረጡ አከባቢዎች ላይ ጥቃት እንዲፈጸም ተንቀሳቅሰው የነበረ ቢሆንም ይሄን የጥፋት ሴራ እና ድርጊት እንዲከሽፍ ማድረግ ተችሏል። ‎በተመሳሳይ በኦሮሚያ ክልል የሸኔ ሽብር ቡድን ከጽንፈኛው ፋኖ ታጣቂ ቡድን ጋር በመናበብ በአንዳንድ አካባቢዎች መንገዶችን በመዝጋት እንቅስቃሴ ለማስቆምና ለማስተጓጎል ፍላጎት የተንቀሳቀሰ ቢሆንም በጸጥታ ኃይሉ በተወሰደበት የተጠናከረ እርምጃ ፍላጎቱን ማሳካት አልቻለም። ቡድኑ በፀጥታ ኃይሉ የተወሰደበትን ርምጃ መቋቋም ባለመቻሉ እና ፍላጎቱን ማሳካት ባለመቻሉ ስስ ዒላማዎች ላይ ያተኮረ ርምጃ በመውሰድ የሃይማኖት እና የብሔር ግጭት ለመቀስቀስ በማለም በአርሲ ዞን አሰኮ እና አካባቢው ጥቃት በመፈጸም ሁሉን አይነት የጥፋት ርብርብ ያደረገ ቢሆንም ሁኔታውን በመቆጣጠር ፀጥታ ኃይላችን በእነዚህ ኃይሎች ላይ የተቀናጀ ርምጃ እየወሰደ ይገኛል። መንግሥት መሰል ሥጋቶችን በንቃት በመከታተል ላይ ሲሆን፣ በምርጫው ወቅትም በብዙ የሀገሪቱ አካባቢዎች የተቀነባበሩ ተመሳሳይ ዕቅዶችን በስኬት ማክሸፍ ችሏል። በንጹሐን ዜጎች ላይ የሚፈጸሙ ጥቃቶችን፤ ፍርሃትና ክፍፍልን ከሚያጎሉ የሚዲያ ዘመቻዎች ጋር በማስተሣሠር የተቀነባበረው ይህ እኩይ ተግባር፤ በመንግሥት የደኅንነት መዋቅርና ኦፕሬሽኖች አማካኝነት በከፍተኛ ሁኔታ እንዲስተጓጎል ተደርጓል። ብሔራዊ እና ሃይማኖታዊ ክፍፍልን ለመዝራት የኃይል ጥቃትን እና ውድመትን እንደ መሣሪያ የሚጠቀሙ አካላት በሁሉም ኢትዮጵያውያን ዘንድ በግልጽ ሊወገዙ ይገባል። መሰል ተግባሮች በኢትዮጵያ ውስጥ ምንም ዓይነት የወደፊት ዕድል እንደሌላቸው ለማሳየት የተቀናጀ ብሔራዊ ምላሽ በመስጠት ወሳኝ ርምጃዎችን ይቀጥላል። ‎በንጹሐን ዜጎች ላይ ጥቃት የሚፈጽሙ አካላት፣ ድርጊታቸውን ምክንያታዊ ለማስመሰል ምንም ዓይነት የፖለቲካ ንግግር ቢጠቀሙ፤ ወሳኝ ዓላማን እያሳኩ ሳይሆን ወንጀል እየፈጸሙ ነው። የፖለቲካ ቅሬታዎች በኢትዮጵያ ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓት፣ በብሔራዊ ምክክር ሂደት እና በዴሞክራሲያዊ ተቋማት አማካኝነት መፍትሔ ሊያገኙ የሚችሉ እና ሊያገኙ የሚገባቸው ናቸው። ‎ ‎ ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! // #PMOEthiopia"

የዲላ ከተማ የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት ከ9 ሰዓት በፊት
Facebook post image 1 Facebook post image 2 Facebook post image 3
Facebook post image 4
+8

"ህብረተሰቡ በኤች.አይ.ቪ ኤድስ ዙርያ ከሚስተዋሉ መዘናጋቶች በመውጣት ስርጭቱን ለመግታት የሚደረጉ ጥረቶችን እንዲያግዝ ተጠየቀ ዲላ፡ግንቦት 28 ፣2018 ዓ.ም የዲላ ከተማ ጤና መምሪያ የቫይራል ሎድ አፈጻጸም ግምገማ ፣ የኤች.አይ.ቪ ኤድስ ስጋት መፈተኛ መሳሪያ ( HRST ) እና በጾታ ላይ በተመሰረተ ጥቃት (GBV) ግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አካሂዷል። በወቅቱ የኤች.አይ.ቪ ኤድስ ስርጭትን ለመግታት የቅድመ መከላከል እና ልየታ ተግባርን ማጠናከር ወሳኝ መሆኑን ነው የተመላከተው። የዲላ ከተማ ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ ዮናስ ዋቀየሁ በወቅቱ እንዳሉት መምሪያው የኤች.አይ.ቪ ኤድስ መካከልና መቆጣጠር ተግባር በትኩረት እያከናወነ እንደሚገኝ ገልጸዋል። የዛሬው ግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናም ይህንኑ ተግባር ለማጠናከር ያለመ መሆኑን የጠቀሱት ኃላፊው በተለይም ቫይረሱ በደማቸው የሚገኙ ወገኖችን በውስጣቸው ያለውን ቫይረስ መጠን ለመቆጣጠር ያስችላል ብለዋል። ከዚህ ጎን ለጎንም ከኤች.አይ.ቪ ስርጭት ጋር ቀጥተኛ ትስስር ያለውን በጾታ ላይ የተመሰረተ ጥቃት (GBV) ለመከላከል የተቀናጀ ስራ እንደሚያስፈልግም አሳስበዋል። መምሪያው በቀጣይም መሰል የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኮችን በማዘጋጀት በቫይረሱ ዙሪያ የህብረተሰቡን ንቃተ-ህሊና ለማሳደግና ተጋላጭነትን ለመቀነስ በትኩረት እንደሚሰራ ገልጸዋል። በዲላ ከተማ የኤችአይቪ ኤድስ ሰርቪስ ባለሙያ የሆኑት አቶ ማርቆስ ዘውዴ ዲላ ከተማ አምራች እና ሀገር አቋራጭ መንገድ ላይ የምትገኝ በመሆኗ የቫይረሱ ተጋላጭነት እንደሚጨምር ተናግረዋል። ይህንንም በመገንዘብ የቫይረሱን ስርጭት ለመቆጣጠር እና ለመከላከል እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው ህብረተሰቡ እራሱን ተመርምሮ በማወቅ የበሽታውን ስርጭት ለመግታት የሚደረጉ ጥረቶችን ማገዝ አለበት ብለዋል። በስልጠናው የታደሙት የሴሳ ክፍለ ከተማ ማህበራዊ ክላስተር ኃላፊ ወይዘሮ መስከረም ህርቤና የሚችሌ ክፍለ ከተማ ማህበራዊ ክላስተር ኃላፊ ወይዘሮ እታፈራው መኩርያ ስልጠናው በቫይረሱ ስርጭት መከላከል ዙርያ ዘርፈ ብዙ ግንዛቤ ያገኙበት እንደሆነ ተናግረዋል። ከስልጠናው ያገኙትን ክህሎት መነሻ በማድረግም በክፍለ ከተሞቻቸው ኤችአይቪ ኤድስ ቫይረስን ለመከላከል ህብረተሰቡን በማስተባበር በቁርጠኝነት እደሚሠሩ ጠቅሰዋል።"

የዲላ ከተማ የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት ከ1 ቀን በፊት
Facebook post image 1 Facebook post image 2 Facebook post image 3
Facebook post image 4
+1

"ምክር ቤቱ የተለያዩ ረቂቅ አዋጆችን መርምሮ አጸደቀ ግንቦት 27/2018 ዓ.ም የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው 23ኛ መደበኛ ጉባኤ የተለያዩ ረቂቅ አዋጆችን መርምሮ አፀደቀ። በኢትዮጵያ መንግሥት እና በሩሲያ ፌዴሬሽን መካከል የጋራ የባዮሎጂ ምርምር ማዕከል ለማቋቋም የቀረበ ረቂቅ አዋጅ መርምሮ አፅድቋል። የውጭ ግንኙነት እና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ ፈትሂ ማህዲ( ዶ/ር ) የውሳኔ ሃሳብና ሪፖርት በዝርዝር አቅርበዋል። የቋሚ ኮሚቴው ምክትል ሰብሳቢ በኢትዮጵያና በሩሲያ ፌዴሬሽን መካከል የጋራ ባዮሎጂካል ምርምር ማዕከል ለማቋቋም የተፈረመው ስምምነት በሁለቱ ሀገራት መካከል የጋራ ሳይንሳዊ እና ጥናታዊ የምርምር ስራዎችን ለማጠናከርና ለማሳደግ እንደሚያግዝ አስረድተዋል፡፡ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የምርምር መሰረተ ልማት ግንባታ እንዲሁም የምርምር ውጤትን ወደ ገበያ የማቅረብ ተቋማዊ ቅርጽ በማስያዝ የሁለቱ ሀገራት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ እንደሚያስችል ምክትል ሰብሳቢው አያይዘው ገልጸዋል፡፡ የሀገር በቀል የኢኮኖሚ እድገትን ለማፋጠን የዓሳ ሀብት ልማት ከፍተኛ ፋይዳ ያለው እንደመሆኑ ኢትዮጵያ ከራሷ አልፎ ወደ ውጭ ኤክስፓርት ለማድረግ ሩሲያ በዘርፉ ካላት ከፍተኛ ልምድ ለማካበት እንደሚያግዝ አስገንዝበዋል። በመሆኑም በኢ.ፌ.ዴ.ሪ. መንግሥት እና በሩሲያ ፌዴሬሽን መካከል የጋራ የባዮሎጂ ምርምር ማዕከል ለማቋቋም የተፈረመው ስምምነት ረቂቅ አዋጅ ፣አዋጅ ቁጥር 1421/2018 ሆኖ በሙሉ ድምፅ ጸድቋል። በተመሳሳይ በኢ.ፌ.ዴ.ሪ. መንግሥት እና በቬትናም ሶሻሊስት ሪፐብሊክ መንግሥት መካከል የዲፕሎማቲክ ወይም ኦፊሻል የአገልግሎት ፓስፖርት ለያዙ ሰዎች ቪዛን ለማስቀረት የተፈረመ ስምምነት ረቂቅ አዋጅን መርምሮ አፅድቋል። የውጭ ግንኙነት እና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ ፈትሂ ማህዲ (ዶ/ር ) የውሳኔ ሃሳብና ሪፖርት በዝርዝር አቅርበዋል፡፡ ምክትል ሰብሳቢው በኢ.ፌ.ዴ.ሪ. መንግሥት እና በቬትናም ሶሻሊስት ሪፐብሊክ መንግሥት መካከል የዲፕሎማቲክ ወይም ኦፊሻል የአገልግሎት ፓስፖርት ለያዙ ሰዎች ቪዛን ለማስቀረት የተፈረመው ስምምነት በሁለቱ ሀገራት መካከል እያደገ የመጣውን የሁለትዮሽ ትብብርንና የዲፕሎማሲ ግንኙነት መስመርን ለማጠናከር የሚያስችል የሕግ ማዕቀፍ የሚፈጥር መሆኑን አስረድተዋል። እንዲሁም ቪዛ ለማግኘት የሚያስፈልጉትን ቅድመ -ሁኔታዎችና የሚወስደውን ጊዜ በማስቀረት የዲፕሎማቲክ ወይም ኦፊሻል እና አገልግሎት ፓስፖርት የያዙ የሁለቱ አገራት ከፍተኛ የመንግሥት ባለስልጣናትና ዲፕሎማቶች እንዲሁም ዜጎች በየጊዜው የሚያደርጉት እንቅስቃሴና ጉዞ በቀላሉ እንዲመቻች የሚያደርግ መሆኑን አያይዘው ተናግረዋል። በመሆኑም በኢ.ፌ.ዴ.ሪ. መንግሥት እና በቬትናም ሶሻሊስት ሪፐብሊክ መንግሥት መካከል የዲፕሎማቲክ ወይም ኦፊሻል የአገልግሎት ፓስፖርት ለያዙ ሰዎች ቪዛን ለማስቀረት የተፈረመው ስምምነት ረቂቅ አዋጅ አዋጅ ቁጥር 1422/2018 ሆኖ በሙሉ ድምፅ መጽደቁን የምክር ቤቱ መረጃ ያመላክታል።"

የዲላ ከተማ የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት ከ1 ቀን በፊት
Facebook post image 1 Facebook post image 2 Facebook post image 3
Facebook post image 4
+4

"የዲላ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ የ7ኛውን ሃገራዊ ምርጫ ስራዎች ማጠቃለያ ግምገማ አካሄደ ዲላ ግንቦት 27/2018ዓም የዲላ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት በከተማዋ የተከናወኑ የ7ኛውን ሃገራዊ ምርጫ ስራዎችን በስኬት ማጠናቀቁን አስመልክቶ የብልጽግና ፓርቲ ኮሚቴ የማጠቃለያ ግምገማ መድረክ አካሂዷል። መድረኩን የመሩት የዲላ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ ቤት ኃላፊ አቶ መንግስቱ ተክሌ በሰጡት ማብራሪያ፤ የዘንድሮው ምርጫ ከመራጮች ምዝገባ ጀምሮ እስከ ድምጽ መስጫ ሂደት ድረስ ከፍተኛና የነቃ የህዝብ ተሳትፎ የታየበት እንደነበር ገልጸዋል። ፓርቲው አስቀድሞ አስቀምጧቸው የነበሩት መንታ ግቦች ሙሉ በሙሉ ስኬታማ መሆናቸውን የገለጹት ኃላፊው፤ አጠቃላይ የምርጫው ሂደት ሰላማዊ፣ ነፃ፣ ፍትሃዊና ተዓማኒ ሆኖ መጠናቀቁን አብራርተዋል። ከምርጫው ጎን ለጎን የልማትና መደበኛ የመንግስት ስራዎች በከተማዋ የምርጫው ሂደት ሲከናወን በነበረው ወቅት የመንግስትን መደበኛ ስራዎች ለአንድም ቀን እንኳ ሳይቋረጥና ልክ ምርጫ እንደሌለ ተደርጎ በከፍተኛ ቁርጠኝነት መሠራቱ በመድረኩ ተገልጿል። ከዚህም ጋር ተያይዞ ከምርጫው ጎን ለጎን በርካታ የህዝብ ጥያቄዎች የተመለሱባቸው የልማት ስራዎች የከተማዋን ገጽታ የሚቀይሩ የኮሪደር ስራዎች በትኩረት መከናወኑ፣ ሰፊ የውስጥ ለውስጥ የመንገድ ከፈታ መሠረተ ልማት ስራዎች መሰራቱ፣ ለረጅም ጊዜ የመብራት ጥያቄ የነበረባቸው አካባቢዎች ዘላቂ ምላሽ እንዲያገኙ መጠነ ሰፊው የአገልግሎት አቅርቦት ምላሽ የመስጠት ስራ መሰራቱ አቶ መንግስቱ ተክሌ አስገንዝበዋል። የዲላ ከተማ ፖለቲካና አቅመ ግንባታ ዘርፍ ኃላፊና ረዳት የመንግስት ተጠሪ ወ/ሮ የካቲት ጥላሁን እንዳሉት የምርጫው ሂደት በብሄራዊ ምርጫ ቦርድ የተቀመጡ የዲስፕሊን መመሪያዎችን በጠበቀ መልኩ መከናወኑንና ከምርጫ ጣቢያዎች ዝግጅት፣ ከመራጮች ምዝገባ እና ከቅስቀሳ ጀምሮ እስከ ድምጽ መስጫ ሂደት ድረስ ህግና መመሪያን በመከተል አጠቃላይ ስራዎች በስኬት መጠናቀቁን አብራርቷል። ወ/ሮ የካቲት አያይዛ በተለይም በከተማው ውስጥ አንድ የጋራ ምክር ቤት መመስረት መቻሉ፣ ከተፎካካሪ ፓርቲዎች ጋር በጠረጴዛ ዙሪያ በምክክርና በውይይት ላይ የተመሰረተውን ስርዓት በማጠናከር የምርጫው ሂደቱን ስኬታማ ለማድረግ ትልቅ አስተዋጽኦ አበርክቷል ስትል ተናግራለች። የዲላ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ አደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊና ረዳት የመንግሥት ተጠሪ በበኩላቸው፤ በከተማዋ ከዚህ በፊት ከነበሩት ምርጫዎች በተለየ መልኩ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ተፎካካሪ ፓርቲዎች መሳተፋቸው የዲሞክራሲ ምህዳሩ መስፋቱና የመድብለ ፓርቲ ስርዓት መጎልበቱን ጠቁመዋል። በተፎካካሪ ፓርቲዎች መካከል የነበረው የፉክክር መንፈስ የከተማዋን የዲሞክራሲ ምህዳር በከፍተኛ ደረጃ ያሰፋው መሆኑን ገልጸዋል። እስከአሁን በቅድመ ምርጫ፣ በምርጫ ዕለትና በድህረ ምርጫ የነበሩ ተግባራት በዲላ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ዲሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ በአቶ ኢሳያስ ተፈራ ሪፖርቱ ቀርቧል። በተለይም በከተማዋ በተደራጁ 60 ምርጫ ጣቢያዎች የከተማዋ ነዋሪዎችና መራጮች እስከ እኩለ ሌሊት ድረስ በጽናት በመሰለፍ ድምጻቸውን የሰጡ ሲሆን፤ ይህ የህዝቡ ቁርጠኝነት ጠንካራ ሀገረመንግስት ለመገንባት የተደረገ ታላቅ አሻራ መሆኑ በመድረኩ ተመላክቷል። ለዚህ ታሪካዊ ምርጫ ስኬታማነት የከተማዋ ወጣቶችና ሴቶች፣ መላው የፓርቲው አባላትና አመራሮች፣ ምሁራንና የንግዱ ማህበረሰብ፣ የፍትህና የፀጥታ ተቋማት ያበረከቱት አስተዋጽኦ የላቀ እንደነበር መገለጹን የፓርቲ ሚዲያና ህዝብ ግንኙነት ዘግቧል።"

የዲላ ከተማ የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት ከ2 ቀን በፊት
Facebook post image 1 Facebook post image 2 Facebook post image 3
Facebook post image 4
+1

"የክልሉ መስተዳድር ምክር ቤት በ30ኛ መደበኛ ጉባኤው በቀጣይ 30 ቀናት እቅድ ስራዎች ዙሪያ በመምከር አቅጣጫ አስቀመጠ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት መስተዳድር ምክር ቤት በበይነ መረብ ባካሄደው 30ኛ መደበኛ ጉባኤው ከምርጫ ማግስት ባለው የአንድ ወር የቅድመ መንግስት ምስረታ ወቅት በሚከናወኑ የቀጣይ የአንድ ወር ስራዎች ዕቅድ ዙሪያ በመምከር ቀጣይ አቅጣጫን አስቀምጧል፡፡ በጉባኤው የክልሉን መንግስት የ2018 ያለፉ አስር ወራት አጠቃላይ ስራዎች ዕቅድ አፈፃፀም እንዲሁም እንደ ሀገር በወጥነት ለማሳካት የታለሙ ሀገራዊ የልማት ኢንሼቲቮች ታሳቢ ያደረገ የቀጣይ የአንድ ወር ስራዎች መሪ ዕቅድ ቀርቦ ሰፊ ውይይት ተደርጎበታል፡፡ ርዕሰ መስተዳድሩ በውይይቱ ወቅት፡- በ7ኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ ህዝቡ በቅድመ ምርጫና በምርጫው ሂደት ያሳየው አስደናቂ ንቁ ተሳትፎ እንዲሁም በድህረ ምርጫው የታየው ስክነትና ጨዋነት ምርጫው ፍጹም ሰላመዊ በሆነ መንገድ ዴሞክራሲያዊ ሂደቱን ጠብቆ በስኬት እንዲጠናቀቅ ማስቻሉን ገልፀው፤ ዕውቅናና ምስጋና ይገባዋል ሲሉ ተናግረዋል፡፡ በቅድመ ምርጫው የተሰሩ ስራዎች ሀገራዊ ምርጫውን እጅግ ሰላማዊ፤ ነፃ፤ ፍትሃዊ፣ ታአማኒ እና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ በስኬት እንዲጠናቀቅ አስትዋፅኦ ማበርከቱን ጠቅሰው፤ የህዝቡን ሰላማዊና ጨዋነት የተሞላው ተሳትፎን ጨምሮ በሂደቱ የድርሻቸውን ለተውጡ አካላት በሙሉ ምስጋና አቅርበዋል፡፡ ርዕሰ መስተዳድሩ አጠቃላይ የምርጫው ውጤት በብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ተገልጾ የመንግስት ምስረታ እስከሚካሄድ ምንም መዘናጋት ሳይፈጠር በምርጫው አስደናቂ አኩሪ ተግባር የፈጸመው ህዝባችንን በልማትና በመልካም አስተዳደር ስራዎች ለመካስ በልዩ ትኩረት መስራት እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡ ለዚህም የተጀመሩ የልማት ተግባራትን በማጠናከር ለህዝብ አዳጊ የልማት ጥያዌዎች ምላሽ መስጠት የሚያስችል በየዘርፉ የአንድ ወር እቅድ በማቀድ ለተግባራዊነቱ መረባረብ እንደሚገባ ተናግረዋል። አክለው እቅዱ በተለይ በክብር ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፤ በየዘርፉ እምርታ ለማስመዝገብ እንደ ሀገር የተቀመጡ ሀገራዊ ግቦችን እንዲሁም በንቅናቄና በመደበኛ የሚመሩና የሚሰሩ ስራዎችን በመለየት እና ያሉ ተጨባጭ አቅሞችን ተጠቅሞ ፈጠራና ፍጥነት በታከለ አፈጻጸም ለውጤት ለማብቃት የሚያስችሉ ስልቶችን ታሳቢ ያደረገ ልሆን እንደሚገባም አስገንዝበዋል፡፡ ርዕሰ መስተዳድሩ የስራዎች አፈጻጸምን ለውጤት ለማብቃት በጠናካራ ድጋፍና ክትትል መደገፍ እንደሚገባም ጠቅሰው፤ በየደረጃው ያለው አመራር ከህዝብና ከመንግስት የተጣለበትን ከፍተኛ ኃላፊነት በአግባቡ በመወጣት፤ በቀሪ ጊዜያት የተሰነቁ ግቦችን ያለምንም መሸራረፍ በመፈጸምና በማስፈጸም የውጤት ዘላቂነትን ማረጋገጥ እንደሚገባው አሳስበዋል፡፡ መስተዳድር ምክር ቤቱ በስብሰባው በቀጣይ 30 ቀናት ሊሳኩ የሚገቡ እና በእጥፍ ለማሳደግ መሰራት የሚገባቸውን ተግባራት በመለየት ቀጣይ አቅጣጫ ያስቀመጠ ሲሆን ከነዚህም፡- * በግብርና ልማት ዘርፍ በቀሪ የበልግና የቀጣይ የመኸር እርሻ ስራዎች ምርታማነትን የማሳደግ፤ በሌማት ትሩፋት በእጥፍ የማብዛት እንዲሁም ለአረንጓዴ አሻራ ስራዎች በትኩረት መስራት፤ * የገቢ አሰባሰብ ስራዎችን በልዩ ትኩረት በቅንጅት በመምራትና ኢኮኖሚው ከሚያመነጨው ገቢ ፍትሀዊ ግብር በመሰብሰብ የህዝብ የልማት ጥያቄዎችን በብቃት ለመመለስ የሚስችል የውስጥ አቅምን የማጠናከር ተግባራት፤ * አገልግሎት አሰጣጥ የማዘመን ስራዎችን የማጠናከር በተለይም በዲላ እና በአርባ ምንጭ ከተሞች የተጀመሩ የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ማዕከላት ፈጥኖ በማጠናቀቅ ወደ አገልግሎት ማስገባት፤ እንዲሁም በሁሉም የከተማ አስተዳደሮች እንደየከተሞች ነባራዊ ሁኔታ በማስፋት በክልሉ የአገልግሎት አሰጣጥን በቴክኖሎጂ የተደገፈ፤ ፈጣንና ቀልጣፋ የማድረግ ተግባራት፤ * የተጀመሩ የከተሞች የኮሪደርና የወንዝ ዳርቻ ልማት ስራዎች በማጠናከር ከዳር የማድረስ እንዲሁም የገጠር ኮሪደር ልማትን በሁሉም የገጠር ቀበሌዎች በመጀመር የታለመውን የገጠር ሽግግር ለማሳካት እና የአርሶ አደሩን ህይወት በማሻሻል ተጠቃሚነቱን ለማረጋገጥ በትኩረት መስራት፤ * ለዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ቁልፍ የሆኑ የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ እና የ 5 ሚሊዮን የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና ግቦች ሙሉ በሙሉ ለማሳካት በልዩ ትኩረት መስራት፤ *በቱሪዝም ዘርፍ የክልሉን እምቅ አቅም መጠቀም በሚያስችል አግባብ በሁሉም ዞን እና ሪጂዮ ፖሊስ ከተሞች አዳዲስ የቱሪስት መዳረሻ ማዕከላትን መለየትና ማልማት፣ በኢንዱስትሪ ልማት ዘርፍ የተጀመሩ ተግባራትን ማጠናከር እንዲሁም አዳዲስ ኢንዱስትሪዎችን ለመጀመር የሚስችል ስራዎችን መስራት፤ በአጠቃላይ የኢኮኖሚ ሉዓላዊነት በማረጋገጥ ከተረጂነት የሚያልቅቁ ተግባራት፤ የኑሮ ውድነት ጫናን የመቀነስና ገበያ የማረጋጋት፤ የአደጋ ስጋት ተግባራት እንዲሁም የክልሉን ሰላም ለማፅናት የፀጥታ ስራዎች የማጠናከር ቀጣይ አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ መደበኛ ስብሰባውን አጠናቋል።"

የዲላ ከተማ የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት ከ2 ቀን በፊት
Facebook post image 1 Facebook post image 2 Facebook post image 3
Facebook post image 4
+4

"ክቡር አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) በዲላ ዙሪያ ወረዳ የግብርና ልማት ሥራዎችን ጎበኙ ዲላ፡ግንቦት፣26/2018 የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ክቡር ዶ/ር አበባየሁ ታደሰ በዲላ ዙሪያ ወረዳ ሽገዶ ቀበሌ በመገኘት የግብርና ልማት ሥራዎችን የመስክ ምልከታ አድርገዋል። ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ በመስክ ምልከታው ወቅት በወረዳው እየተከናወኑ ያሉ የቡና ክላስተር ልማት እና የሌማት ትሩፋት ሥራዎች አበረታች መሆናቸውን ጠቁመው ተግባሩ ይበልጥ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አሳስበዋል። የጌዴኦ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና የግብርና መምሪያ ኃላፊ ክቡር አቶ ተገኝ ታደሰ በበኩላቸው፤ በዞን ደረጃ የቡና ምርትና ምርታማነትን ለማሻሻል ለክላስተር ልማትና ለሌማት ትሩፋት ተግባራት ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። በዚህም በዲላ ዙሪያ ወረዳ በቡና ክላስተር ልማት ተጨባጭ ውጤቶች እየተመዘገቡ መሆኑን ጠቁመዋል። አቶ ተገኝ አክለውም የሌማት ትሩፋት ሥራዎች ጅምር የሚበረታታ መሆኑን ገልጸው በቀጣይም በሁሉም አካባቢዎች ይበልጥ ተጠናክረው መሰራት እንዳለባቸው አሳስበዋል። በዚሁ የመስክ ጉብኝት ላይ ክቡር አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ክቡር አቶ ተገኝ ታደሰን ጨምሮ የዞኑ ግብርና መምሪያ ምክትል ኃላፊዎች እንዲሁም የወረዳው ከፍተኛ አመራሮችና አስተባባሪ አካላት መሳተፋቸውን የዲላ ዙሪያ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ዘግቧል።"

የኢንቨስትመንት እድሎች

ከተማዋ ውስጥ ያሉ የኢንቨስትመንት ዘርፎች

በዘርፉ ያሉ እድሎች

አገልገሎቶች

ቅድሚያ የተሰጠው ዘርፍ

እንዱስትሪዎች

ግብርና

ማኑፋክቸሪንግ

ዋና የማስተዋጽኦ አጋጣሚዎች

  • ፈጣን አገልግሎት
ሴክተሮች

መምሪያዎች

የዲላ ከተማ አስተዳደር የሴክተር መ/ቤቶችና ሥራና ኃላፊነት

ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት ጽ/ቤት

ማዘጋጃ ቤታችን የከተማዋን ነዋሪዎች የኑሮ ጥራት ለማሻሻል፣ ጽዱና ለሚኖሩባት ምቹ የሆነች ከተማ ለመፍጠር የተለያዩ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና መሠረተ-ልማታዊ አገልግሎቶችን ይሰጣል። የፕላን መረጃ መስጠት፡መሬቱ ለምን አይነት አገልግሎት (ለቤት፣ ለንግድ፣ ለኢንዱስትሪ...) እንደሚ...
ዝርዝር ይመልከቱ

የመሬት አስተዳደር መምሪያ

መምሪያው በከተማ የሚገኘውን የከተማና የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀምን በበላይነት የማስተዳደርና የመቆጣጠር ኃላፊነት አለበት። በዚህም መሠረት፡-  የከተማ አጠቃላይ የመሬት ካዳስተር ሥርዓት በማዘመን ለዜጎች የይዞታ ማረጋገጫና የባለቤትነት መብት ሰነድ በቀልጣፋና በተመጣጣኝ ዋ...
ዝርዝር ይመልከቱ

የንግድና ኢንዱስትሪ ልማት መምሪያ

መምሪያው በከተማ የንግድና ኢንዱስትሪ ዘርፍ እድገትን በማምራት፣ በማበረታታትና በመቆጣጠር ረገድ ወሳኝ ሚና ይጫወታል። በዚህም መሠረት፡-  ቀልጣፋና ግልጽ የንግድ ምዝገባና ፈቃድ አሰጣጥ አገልግሎት በመስጠት ሕጋዊ የንግድ አካላት እንዲቋቋሙና እንዲስፋፉ ያደርጋል፤  በከተማ ውስጥ...
ዝርዝር ይመልከቱ

የቱሪዝም መምሪያ

መምሪያው የዲላ ከተማን በሀገር ውስጥም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተመራጭ የቱሪስት መዳረሻ ለማድረግ ይተጋል። በዚህም መሠረት፡-  የከተማዉን የቱሪዝም ሀብቶች (ተፈጥሯዊ፣ ባህላዊ፣ ታሪካዊ) በመለየት ካርታ በማዘጋጀትና በማስተዋወቅ ለቱሪስቶች ማራኪ እንዲሆኑ ያደርጋል፤ በከተማ ው...
ዝርዝር ይመልከቱ

የሥራና ክህሎት መምሪያ

መምሪያው በከተማ ውስጥ ምርታማ የሥራ ዕድሎችን በመፍጠርና የሰው ኃይልን ብቃት በማሳደግ ረገድ ማዕከላዊ ሚና ይጫወታል። በዚህም መሠረት፡-  የከተማ የሥራ ገበያ ፍላጎት በማጥናት በቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች የሚሰጠው ሥልጠና ከገበያ ፍላጎት ጋር እንዲጣጣም ያደርጋል፤  የሥራ አጦችን...
ዝርዝር ይመልከቱ

የፋይናንስና ፕላን ልማት መምሪያ

መምሪያው የከተማን የበጀት አዘገጃጀት፣ አፈጻጸምና ቁጥጥር በበላይነት የሚመራ ከፍተኛ አካል ነው። በዚህም መሠረት፡-  የከተማ ዓመታዊ በጀት በማዘጋጀት ለከተማ አስተዳደር ምክር ቤት በማቅረብ ሲፀድቅም አፈጻጸሙን ይከታተላል፤ ከክልል ፋይናንስ ቢሮ ጋር በመተባበር የከተማ የገንዘብ...
ዝርዝር ይመልከቱ

የገቢዎች መምሪያ

መምሪያው በከተማ የሚገኙ የተለያዩ የመንግሥት ገቢዎችን በመሰብሰብና በማስተዳደር ረገድ ወሳኝ ኃላፊነት አለበት። በዚህም መሠረት፡-  በከተማ ውስጥ ተፈጻሚነት ያላቸውን የክልል ታክስና ግብሮች (እንደ በጀት ዓመታዊ ታክስ፣ የንብረት ታክስ፣ ወዘተ) በመለየት በሥርዓት መሰብሰባቸውን...
ዝርዝር ይመልከቱ

የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ መምሪያ

መምሪያው በከተማ የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን በማስፋፋትና የፈጠራ ሥራዎችን በማበረታታት ረገድ ያተኩራል። በዚህም መሠረት፡-  በከተማ የሚገኙ መምሪያዎችና የበታች አስተዳደሮች የኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ (አይሲቲ) አጠቃቀም አቅም እንዲያድግ ድጋፍና ሥልጠና ይሰጣል፤  የከተማ አ...
ዝርዝር ይመልከቱ

ኮርደር ልማት

እንደ ሐገር በከተሞች ብቻ ሳይሆን በገጠርም ጭምር እየተተገበረ የሚገኘው የኮሪደር ልማት ቀድሞ የነበሩ ከተሞችን ገፅታ በመቀየር አዲስ ገፅታን በማላበስ ከተሞችን ውብ ማራኪና ተመራጭ እንዲሆኑ አስችሏል፡፡

የኮሪደር ልማት አዲስ ኢንሼቲቭ እንደመሆኑ በአተገባበር ወቅት ዉስን ተግዳሮቶች ቢያጋጥሙትም አሁን ላይ በመንግስት ብቻ ሳይሆን በሕብረተሰቡ ተሳትፎም ጭምር ተግባራዊ በመደረግ ላይ ይገኛል

ይህ አዲስ ከተማ ፈጣሪ ኢንሼቲቭዲላ ከተማን ለነዋሪዎች ለኑሮ ምቹ እንዲሁም ተወዳደሪ ከተማ ለማድረግ እየተተገበሩ ካሉ ሥራዎች መካከል አንዱ በተመረጡ የከተማዋ አካባቢዎች የመንገድ ኮሪደር ልማት መከወን ነው።

ባለፉት ዓመታት በከተማችን የመንገድ ኮሪደር ልማት የሚከወንባቸው በቁጥር 8 ዋና ዋና ኮሪደሮችን 18 ኪ.ሜትር በላይ በመለየት የፕላን ማስጠበቅ እንዲሁም ዘርፈ ብዙ የኮሪደር ልማት ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ፡

ለኮሪደር ልማት ሥራ የመጀመሪያው ቅድመ ሁኔታ የከተማ ፕላን የማስጠበቅ ሥራ ሲሆን በዚህመ ረገድ በከተማው ነዋሪ ንቁ ተሳትፎ እንዲሁም በየደረጃው ባሉ ባለድርሻ አካላት የተቀናጀ ሥራ ከ19.2 ኪሎሜትር በላይ ፕላን የማስጠበቅ ተግባር ተከናውኗል፡፡

የከተማው ነዎሪዎች በፕላን ማስጠበቅ ተግባሩ ባደረጉት ንቁ ተሳትፎ ከመንግሥት ሊወጣ የነበረውን 654 ሚሊዮን ብር ማዳን የተቻለ ሲሆን 517 ቤቶችን በማፍረስ የከተማ ፕላን ማሰጠበቅ ተግባር በማከናወን ለቀጣይ የመንገድ ኮሪደር ልማት ምቹ ሁኔታ መፍጠር ተችሏል፡፡

ከአዲስ አበባ ሞጆ ኢትዮ ኬኒያ የሚዘልቀው አስፋልት መንገድ አቋርጧት የሚያልፈው  የዲላ ከተማመግቢያበር ላይ እጅግ ሳቢና ማራኪ የመግቢያ ግንባታ የማጠናቀቂያ ሥራ በከናወን ላይ ይገኛል፡፡

በኮሪደር ልማት በመንገድ ዳር አረንጓዴ ልማት 16 ሺህ 700ካሬሜትርተሰርቶ የተጠናቀቀ ሲሆን በተመሳሳይ 8.4 Km እግረኛመንገድ ተጠናቋል፡፡

በቁጥር 5 እስናክሀውስግንባታ ተጠናቅቆ በእዚሁአከባቢ 20 ማረፊያ መቀመጫዎች ተዘጋጅተ ሕብረተሰቡ አረፍ ብሎ ነፋሻ አየር እንዲቀበልና ራሱን እንዲያዝናና አስተዋኦ በማበርከት ላይ ይገኛል፡፡

በከተማው የሚገኙ 2 አደባባዮችን ደረጃውን በጠበቀ መልኩ የማልማት እና የማስዋብ ሥራ ተሰርቶ 4ኪ.ሜ የመንገድ መብራት ማስዋብ ሥራ ተጀምሮ በመጠናቀቅ ላይ ይገኛል፡፡.

የኮሪደር ልማት ከተማን እንደ አዲስ ከነፍጠር ባሻገር ጊዜያዊና ቋሚ የስራ እድል በመፍጠርም አበርክቶቱ ከፍተኛ ሆኖ በዲላ ለ1ሺህ 205 ዜጎች ቋሚና ጊዜያዊ የሥራ ዕድል ተፈጥሯል፡፡

 

የዲላ ከተማ የኮሪደር ልማትን በማስቀጠል በከተማዋ ክልል ዋና ዋና መንገዶች ላይና አደባባዮች ብሎም ሰው ሰራሽ ሐይቅም ጭምር  በመስራት አዲስ ከተማ የመፍጠሩ ተግባር ከነዋሪዎቻችን ጋር እጅ ለእጅ በመያያዝ ተጠናክሮ ይቀጥላል፡፡

ኮርደር ልማት
ኮርደር ልማት
ኮርደር ልማት
ኮርደር ልማት
ኮርደር ልማት
ኮርደር ልማት

ዲላ በለውጥ ምዕራፍ ላይ ናት!

እንኳን ወደ ዲላ ከተማ አስተዳደር ይፋዊ የድረ-ገጽ መረጃ ቋት በሰላም መጣችሁ!

የከተማችን አስተዳደር ኮሚዩኒኬሽን ዋነኛ ዓላማ በመንግስትና በህዝብ መካከል የታመነ ድልድይ በመሆን፣ የዲላን ሁለንተናዊ እንቅስቃሴዎች ለነዋሪዎቻችንና ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ተደራሽ ማድረግ ነው።

ዲላ በለውጥ ምዕራፍ ላይ ናት!

በአሁኑ ወቅት በከተማችን በብልፅግና ፓርቲ መሪነት የሚከናወኑ፦

  • የኮሪደር ልማት ስራዎች፣
  • የውስጥ ለውስጥ መንገዶች ግንባታ እና
  • ሌሎች ግዙፍ የመሠረተ ልማት ስኬቶች የከተማችንን ገጽታ ከመቀየር ባለፈ ለነዋሪዎቻችን ምቹ የኑሮ ሁኔታን እየፈጠሩ ይገኛሉ።

የዲጂታል ሚናችንና ግባችን፦

  1. ወቅታዊ መረጃ፦ የልማት ስራዎችንና የመንግስት ውሳኔዎችን በታማኝነት ማጋራት።
  2. የመረጃ ሉዓላዊነት፦ በከተማችን ሰላምና ልማት ላይ የሚነዙ የተዛቡ መረጃዎችን (Misinformation) በእውነተኛ መረጃ መመከት።
  3. ሁለትዮሽ ግንኙነት፦ የመንግስትን ድምፅ ማስተማር ብቻ ሳይሆን፣ የህዝቡን ቅሬታና ጥቆማ የምንቀበልበት ክፍት መድረክ መሆን።

የክብር ጥሪ፦

የዲላ ከተማ ነዋሪዎችና የከተማችን ወዳጆች በሙሉ፤ ይህንን ድረ-ገጽ እንደ ዋነኛ የመረጃ ምንጭ በመጠቀም ለከተማችን ዕድገትና ሰላም ገንቢ አስተያየታችሁን እንድታካፍሉን ጥሪዬን አቀርባለሁ።

መረጃ የልማት መነሻ ነው!

 

ዲላ በለውጥ ምዕራፍ ላይ ናት!

የፎቶግራፍ አምዶች

የከተማችንን ውበት ያስሱ